News
ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል አወዳድሮ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች ከነሐሴ 05/2017 እስከ ነሐሴ 15/2017 ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለመመዝገን ይህንን ሊንክ መጠቀም ትችላላችሁ።
ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል አወዳድሮ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች ከነሐሴ 05/2017 እስከ ነሐሴ 15/2017 ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለመመዝገን ይህንን ሊንክ መጠቀም ትችላላችሁ።
Aug 08, 2025
238
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይህ ክብረ በዓል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለጎንደርና ለአካባቢው ህዝብ ያለውን ፋይዳ እንዲሁም ህዝቡ ለተቋሙ ያለውን አክብሮት ያየንበት ነው ብለዋል።
በዓሉ ከዩኒቨርሲቲውና ከሆስፒታሉ ምስረታ በላይ በተለይ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የጎንደርን ህዝብ ጥልቅ የሆነ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ያንፀባረቀበትም እንደነበር አንስተዋል።
በተለይም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሁሉም ክልሎች የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን እንደ አንድ የሀገር ልጆች የሚቀበልበት “የጎንደር ቃል ኪዳን ቤተሰብ ፕሮግራም” ለጎንደር ብቻ ሳይሆን ለሀገራችንም ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።
ዩኒቨርስቲዎች አንዱ እንዲያደርጉ የምንፈልገው የመንደር ሳይሆኑ የሀገር ሀብት እንዲሆኑ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ፤
በተለይ አሁን ዋና ሪፎርም ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን እንዲችሉ በነፃነት የሚሰሩ፣ በነፃነት የሚያስቡ እውነትንና እውቀትን የሚፈልጉ ሰዎች የተሰባሰቡባቸው ሰላማዊ ቦታ እንዲሆኑ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም ዩኒቨርስቲዎች በመማር ማስተማር ፣ በጥናትና ምርምር በሚሰሩ ሥራዎች አካባቢያቸውን እንዲረዱ እና የአካባቢውን ፀጋ ተጠቅመው የህዝቡን ህይወት እንዲያሻሽሉ ይጠበቃል ብለዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲው 70ኛ እና ማስተማሪያ ሆስፒታሉ 100ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል ከጥር 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ በስኬት መጠናቀቁን በመግለጽ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተ ጀምሮ ያከናወናቸውን የታሪክ ጉዞ ያነሱት ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ ዩኒቨርስቲው ራስ ገዝ ለመሆን ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል ።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይህ ክብረ በዓል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለጎንደርና ለአካባቢው ህዝብ ያለውን ፋይዳ እንዲሁም ህዝቡ ለተቋሙ ያለውን አክብሮት ያየንበት ነው ብለዋል።
በዓሉ ከዩኒቨርሲቲውና ከሆስፒታሉ ምስረታ በላይ በተለይ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የጎንደርን ህዝብ ጥልቅ የሆነ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ያንፀባረቀበትም እንደነበር አንስተዋል።
በተለይም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሁሉም ክልሎች የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን እንደ አንድ የሀገር ልጆች የሚቀበልበት “የጎንደር ቃል ኪዳን ቤተሰብ ፕሮግራም” ለጎንደር ብቻ ሳይሆን ለሀገራችንም ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።
ዩኒቨርስቲዎች አንዱ እንዲያደርጉ የምንፈልገው የመንደር ሳይሆኑ የሀገር ሀብት እንዲሆኑ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ፤
በተለይ አሁን ዋና ሪፎርም ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን እንዲችሉ በነፃነት የሚሰሩ፣ በነፃነት የሚያስቡ እውነትንና እውቀትን የሚፈልጉ ሰዎች የተሰባሰቡባቸው ሰላማዊ ቦታ እንዲሆኑ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም ዩኒቨርስቲዎች በመማር ማስተማር ፣ በጥናትና ምርምር በሚሰሩ ሥራዎች አካባቢያቸውን እንዲረዱ እና የአካባቢውን ፀጋ ተጠቅመው የህዝቡን ህይወት እንዲያሻሽሉ ይጠበቃል ብለዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲው 70ኛ እና ማስተማሪያ ሆስፒታሉ 100ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል ከጥር 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ በስኬት መጠናቀቁን በመግለጽ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተ ጀምሮ ያከናወናቸውን የታሪክ ጉዞ ያነሱት ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ ዩኒቨርስቲው ራስ ገዝ ለመሆን ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል ።
Aug 06, 2025
92
የትምህርት ሚኒስትሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው በስተላለፉት መልዕክት አሁን ካለንበት የትምህርት ጥራት ችግር ለመውጣት ትልቅ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ሪፎርሞች ተቀርፀው በትምህርት ሴክተሩ እየተተገበሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች ዓለም ያለችበትን ሁኔታ የተገነዘቡ፤ ሀገርን ከችግር ሊያወጡ የሚችሉ ጥናትና ምርምሮች በማድረግ እውነትና እውቀትን መሠረት ያደረገ ነፃ ሀሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ነው ያሉት።
እንደ ህብረተሰብ እንዳንጠፋ ከፈለግን ይህንን የሚቋቋም ትውልድ ለመፍጠር በመሰረታዊነት በመናበብ ከላይ እስከ ታች እነዚህን ሪፎርሞች መተግበር ይገባናል ብለዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲኖረን እንፈልጋለን ያሉት ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል የሚኖር ውድድር በሚሰጡት የትምህርት ጥራት እና በሚሰሯቸው ጥናትና ምርምሮች ብቻ መሆን እንዳለበትም አሳስበዋል።
አክለውም ብቃት ያላቸው ተማሪዎች በጋራ ተሰብስበው ብቃት ባላቸው መምህራን የሚማሩበት ከባቢ በዩኒቨርስቲዎች እንዲፈጠር እንፈልጋለንም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ይህ የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ወዴት እየሄደ ነው፤ እንዴት ሪፎርሙ መተግበር እንችላለን የሚለውን ማየት የተቻለበት ነው ብለዋል።
የቁልፍ ተግባራት አፈፃፀምም ዩኒቨርሲቲዎችን ደረጃ ለማውጣት ሳይሆን ዩኒቨርሲቲዎቹ ምን ደረጀ ላይ ናቸው የሚለውን ያየንበት ነበር ያሉ ሲሆን
በአጠቃላይ ለሁለት ቀናት የቆየው ጉባኤ በትምህርት ስርዓቱ ላይ እየተደረገ ስላለው ለውጥ የጋራ መግባባት ላይ የተደረሰበት እንደሆነም ተናግረዋል።
''የከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ተፅዕኖ" በሚል በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያን የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤም ተጠናቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው በስተላለፉት መልዕክት አሁን ካለንበት የትምህርት ጥራት ችግር ለመውጣት ትልቅ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ሪፎርሞች ተቀርፀው በትምህርት ሴክተሩ እየተተገበሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች ዓለም ያለችበትን ሁኔታ የተገነዘቡ፤ ሀገርን ከችግር ሊያወጡ የሚችሉ ጥናትና ምርምሮች በማድረግ እውነትና እውቀትን መሠረት ያደረገ ነፃ ሀሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ነው ያሉት።
እንደ ህብረተሰብ እንዳንጠፋ ከፈለግን ይህንን የሚቋቋም ትውልድ ለመፍጠር በመሰረታዊነት በመናበብ ከላይ እስከ ታች እነዚህን ሪፎርሞች መተግበር ይገባናል ብለዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲኖረን እንፈልጋለን ያሉት ሚኒስትሩ ከዚህ በኋላ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል የሚኖር ውድድር በሚሰጡት የትምህርት ጥራት እና በሚሰሯቸው ጥናትና ምርምሮች ብቻ መሆን እንዳለበትም አሳስበዋል።
አክለውም ብቃት ያላቸው ተማሪዎች በጋራ ተሰብስበው ብቃት ባላቸው መምህራን የሚማሩበት ከባቢ በዩኒቨርስቲዎች እንዲፈጠር እንፈልጋለንም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ይህ የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ወዴት እየሄደ ነው፤ እንዴት ሪፎርሙ መተግበር እንችላለን የሚለውን ማየት የተቻለበት ነው ብለዋል።
የቁልፍ ተግባራት አፈፃፀምም ዩኒቨርሲቲዎችን ደረጃ ለማውጣት ሳይሆን ዩኒቨርሲቲዎቹ ምን ደረጀ ላይ ናቸው የሚለውን ያየንበት ነበር ያሉ ሲሆን
በአጠቃላይ ለሁለት ቀናት የቆየው ጉባኤ በትምህርት ስርዓቱ ላይ እየተደረገ ስላለው ለውጥ የጋራ መግባባት ላይ የተደረሰበት እንደሆነም ተናግረዋል።
''የከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ተፅዕኖ" በሚል በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያን የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤም ተጠናቋል።
Aug 05, 2025
61
በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ይህ ጉባኤ በትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምን ያህል ለውጥ ተመዘገበ ተብሎ የሚገመገምበትና የወደፊት አቅጣጫ የሚቀመጥበት መሆኑን ገልፀዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወዳዳሪ፣ የበለፀገች፣ ሉዓላዊት፣ ዴሞክራሲያዊት እና ፍትሃዊ የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ሚናቸው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም "የትምህርት ጥራት የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በገቡት የቁልፍ ተግባራት መለኪያ ውል መሠረት ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩና ባልተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ለመመካከር እድል ይፈጥራል ብለዋል።
በተጨማሪም መድረኩ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ልምድ ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አሥራት አጸደወይን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ እና የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ100ኛ ዓመት በሚከበርበት ወቅት በመሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው ገልፀው ለዚህም አመሥግነዋል።
ዩኒቨርሲቲዎችን የራስ ገዝ ለማድረግ የሚካሄደው ለውጥ የሚደነቅ መኾኑን አንስተው የጎንደር ዩኒቨርሲቲም ራስ ገዝ ለመሆን እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአዲስ አሠራር እና የለውጥ ሐዋርያ ናቸው ያሉት ፕሬዚዳንቱ ለዚህም በትብብር መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ የትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኀላፊዎች ፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ፤ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብትና ቴክኖሎጅ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፤ የመምህራን ማኅበር የሥራ ኀላፊዎች ፤ የከፍተኛ ትምህርት የተማሪ ኅብረት ኀላፊዎችና ተጠሪ ተቋማት ተገኝተዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ይህ ጉባኤ በትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምን ያህል ለውጥ ተመዘገበ ተብሎ የሚገመገምበትና የወደፊት አቅጣጫ የሚቀመጥበት መሆኑን ገልፀዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወዳዳሪ፣ የበለፀገች፣ ሉዓላዊት፣ ዴሞክራሲያዊት እና ፍትሃዊ የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ሚናቸው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም "የትምህርት ጥራት የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በገቡት የቁልፍ ተግባራት መለኪያ ውል መሠረት ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩና ባልተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ለመመካከር እድል ይፈጥራል ብለዋል።
በተጨማሪም መድረኩ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ልምድ ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አሥራት አጸደወይን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ እና የአጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ100ኛ ዓመት በሚከበርበት ወቅት በመሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው ገልፀው ለዚህም አመሥግነዋል።
ዩኒቨርሲቲዎችን የራስ ገዝ ለማድረግ የሚካሄደው ለውጥ የሚደነቅ መኾኑን አንስተው የጎንደር ዩኒቨርሲቲም ራስ ገዝ ለመሆን እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአዲስ አሠራር እና የለውጥ ሐዋርያ ናቸው ያሉት ፕሬዚዳንቱ ለዚህም በትብብር መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ የትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኀላፊዎች ፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ፤ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብትና ቴክኖሎጅ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፤ የመምህራን ማኅበር የሥራ ኀላፊዎች ፤ የከፍተኛ ትምህርት የተማሪ ኅብረት ኀላፊዎችና ተጠሪ ተቋማት ተገኝተዋል።
Aug 04, 2025
57
ስልጠናውን መስጠት ከጀመሩ ዩኒቨርስቲዎች አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዲን የቆየዓለም ደሴ (ዶ/ር) ዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን በጥሩ ሁኔታ ለማሰልጠን የአሰልጣኝ መምህራን ፣ የስልጠና ክፍሎች፣ የተማሪዎች ማደሪያ ፣ የካፍቴሪያ እና የማሰልጠኛ ሞጁልና ምዝገባ አጠናቆ ስልጠና መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው መምህራን በሚያስተምሩበት ትምህርት ዓይነት ፣ በማስተማር ስነ ዘዴ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁም በስነ ልቦናዊ ፣ ማህበራዊና የጤና ጉዳዮችን አካቶ የያዘና ሰፊ ክፍተትን የሚሞላ በመሆኑ ሰልጣኞች ተረጋግተው መሰልጠንና የመጡበትን አላማ ሳይረሱ ክፍል ውስጥም ሆነ ከሌሎች ጓደኞቻቸውና ከአሰልጣኝ መምህራን ጋር መነጋገር እና መማር እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በዩኒቨርስቲው ያገኘናቸው የስልጠና አስተባባሪ አቶ ታደሰ ተሬሳ በበኩላቸው ለሰልጣኝ የ2ኛ ደረጃ መምህራንና የት/ቤት አመራሮች በዩኒቨርስቲው አቀባበል እንደተደረገላቸው ጠቁመው ሰልጠናውንም በሚመለከት ገለጻ የተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ስልጠናው የመመህራኑንና አመራሮቹን አቅም በማጎልበት የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻልና በትምህርት ላይ ያሉ ቸግሮችን በመፍታት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በስልጠናው ላይ የገኘናት የፋና 02 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የኢኮኖሚክስ መምህርት ኩመሌ አበራ በሰጠችው አስተያየት ስልጠናው ከዚህ በፊት ከነበራት እውቀትና ክህሎት በተጨማሪ ተጨባጭ እውቀት ፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ፣ የማስተማር ስነ ዘዴ ክህሎት አገኛለሁ ብላ እንደምትጠብቅ ተናግራለች፡፡
የጣፎ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርት ዘውዲቱ ሰቦቃ በበኩሏ ባለፈው ዓመት የሰለጠኑ መምህራን የማስተማር ተነሳሽነትና ፍላጎት ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሳ ስልጠናው ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርላትና ተነሳሽነቷንም የበለጠ እንደሚያሳድግላት ገልጻለች፡፡
የቀራንዮ አንደኛና መካከለኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርአሰ መምህር አህመድ በዳሶ በዚሁ ጊዜ በሰጠው አስተያየት ስልጠናውን በሙሉ ልብ ለመውሰድ ሰው ወክሎና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ መምጣቱን ገልጾ ከስልጠናው ብዙ ለውጦችን አግኝቶ ክፍተቱን እንደሚሞላ ተናግሯል፡፡
ስልጠናውን መስጠት ከጀመሩ ዩኒቨርስቲዎች አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዲን የቆየዓለም ደሴ (ዶ/ር) ዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን በጥሩ ሁኔታ ለማሰልጠን የአሰልጣኝ መምህራን ፣ የስልጠና ክፍሎች፣ የተማሪዎች ማደሪያ ፣ የካፍቴሪያ እና የማሰልጠኛ ሞጁልና ምዝገባ አጠናቆ ስልጠና መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው መምህራን በሚያስተምሩበት ትምህርት ዓይነት ፣ በማስተማር ስነ ዘዴ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁም በስነ ልቦናዊ ፣ ማህበራዊና የጤና ጉዳዮችን አካቶ የያዘና ሰፊ ክፍተትን የሚሞላ በመሆኑ ሰልጣኞች ተረጋግተው መሰልጠንና የመጡበትን አላማ ሳይረሱ ክፍል ውስጥም ሆነ ከሌሎች ጓደኞቻቸውና ከአሰልጣኝ መምህራን ጋር መነጋገር እና መማር እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በዩኒቨርስቲው ያገኘናቸው የስልጠና አስተባባሪ አቶ ታደሰ ተሬሳ በበኩላቸው ለሰልጣኝ የ2ኛ ደረጃ መምህራንና የት/ቤት አመራሮች በዩኒቨርስቲው አቀባበል እንደተደረገላቸው ጠቁመው ሰልጠናውንም በሚመለከት ገለጻ የተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ስልጠናው የመመህራኑንና አመራሮቹን አቅም በማጎልበት የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻልና በትምህርት ላይ ያሉ ቸግሮችን በመፍታት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በስልጠናው ላይ የገኘናት የፋና 02 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የኢኮኖሚክስ መምህርት ኩመሌ አበራ በሰጠችው አስተያየት ስልጠናው ከዚህ በፊት ከነበራት እውቀትና ክህሎት በተጨማሪ ተጨባጭ እውቀት ፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ፣ የማስተማር ስነ ዘዴ ክህሎት አገኛለሁ ብላ እንደምትጠብቅ ተናግራለች፡፡
የጣፎ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርት ዘውዲቱ ሰቦቃ በበኩሏ ባለፈው ዓመት የሰለጠኑ መምህራን የማስተማር ተነሳሽነትና ፍላጎት ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሳ ስልጠናው ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርላትና ተነሳሽነቷንም የበለጠ እንደሚያሳድግላት ገልጻለች፡፡
የቀራንዮ አንደኛና መካከለኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርአሰ መምህር አህመድ በዳሶ በዚሁ ጊዜ በሰጠው አስተያየት ስልጠናውን በሙሉ ልብ ለመውሰድ ሰው ወክሎና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ መምጣቱን ገልጾ ከስልጠናው ብዙ ለውጦችን አግኝቶ ክፍተቱን እንደሚሞላ ተናግሯል፡፡
Aug 04, 2025
53
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በምክክሩ ወቅት እንደገለጹት ለፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዋጅ የተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች በውጤታማነት እንዲፈጸሙ በተደራጀና በተቀባጀ አግባብ መምራት እንደሚባ አመላክተዋል፡፡
የዩኒቨርስቲ የስራ አመራር ቦርድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ተግባርና ኃላፊነቶቻቸውን ብሎም የሚተገብሯቸውን የሪፎርም ስራዎች በውጤታማነት መፈጸምና ማከናወን እንዲችሉ የስራ አመራር ቦርድ የአሰራር ማኑዋለል መዘጋጀቱን ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል፡፡
ይህም ተቋማቱ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጡ እንደሚያስችላቸውና ተጨማሪ አቅምና አደረጃጀት የሚፈጥርላቸው መሆኑንም ክቡር አቶ ኮራ አስረድተዋል፡፡
የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው የስራ አመራር ማኑዋሉም ሆነ የአፈጻጸም ግምገማ መስፈርቶቹ የተፈጻሚነት ወሰን ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ አመራር ቦርድ የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በቀጣይ ተቋማቱን በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ ለመደገፍ የስራ አመራር ቦርዱ ሰብሳቢውን ጨምሮ እስከ አስራ አንድ የሚደርሱ አባላት እንዲኖሩት መታሰቡን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
በምክክር መድረኩም ላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ምክትል ስራ አመራር የቦርድ አባላት፣የከፍተኛ ትምሀርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች ፣ የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በምክክሩ ወቅት እንደገለጹት ለፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዋጅ የተሰጡ ተግባርና ኃላፊነቶች በውጤታማነት እንዲፈጸሙ በተደራጀና በተቀባጀ አግባብ መምራት እንደሚባ አመላክተዋል፡፡
የዩኒቨርስቲ የስራ አመራር ቦርድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ተግባርና ኃላፊነቶቻቸውን ብሎም የሚተገብሯቸውን የሪፎርም ስራዎች በውጤታማነት መፈጸምና ማከናወን እንዲችሉ የስራ አመራር ቦርድ የአሰራር ማኑዋለል መዘጋጀቱን ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል፡፡
ይህም ተቋማቱ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጡ እንደሚያስችላቸውና ተጨማሪ አቅምና አደረጃጀት የሚፈጥርላቸው መሆኑንም ክቡር አቶ ኮራ አስረድተዋል፡፡
የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው የስራ አመራር ማኑዋሉም ሆነ የአፈጻጸም ግምገማ መስፈርቶቹ የተፈጻሚነት ወሰን ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ አመራር ቦርድ የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በቀጣይ ተቋማቱን በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ ለመደገፍ የስራ አመራር ቦርዱ ሰብሳቢውን ጨምሮ እስከ አስራ አንድ የሚደርሱ አባላት እንዲኖሩት መታሰቡን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
በምክክር መድረኩም ላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ምክትል ስራ አመራር የቦርድ አባላት፣የከፍተኛ ትምሀርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች ፣ የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
Aug 02, 2025
47
የትምህርት ሚኒስትሩ በሰጡት ማሳሰቢያ ለሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና ስኬታማነት የዩኒቨርስቲ አመራሮች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን ስልጠና የሚሰጡ 30 ዩኒቨርስቲዎች ሰልጣኝ መምህራንንና የትምህርት ቤት አመራሮችን በአግባቡ በመቀበልና በማሰልጠን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
አክለውም የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና ለትምህርት ጥራት ወሳኝ በመሆኑ ዩኒቨርስተዎች መምህራኑና አመራሮቹ የተዘጋጀላቸውን የስልጠና ሞጁል መጨረሳቸውን ፣ስልጠናውንም በአግባቡ መከታተላቸውንና መመዘናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና በአግባቡ እንዲጠናቀቅ የዩኒቨርስቲ አመራሮችና ኃላፊዎች ድጋፍና ትብብር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የተውጣቱ ከ84ሺ የሚበልጡ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች በሚያተምሩት የትምህርት ዓይነት ላይ መሰረት ያደረገ ስልጠና ወስደው ከተመዘኑ በኋላ የምስክር ወረቀት እንደሚሰጣቸው በመድረኩ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ከ52 ሺ የሚበልጡ የ2ኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት ስልጠና መውሰዳቸውንም ይታወሳል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ በሰጡት ማሳሰቢያ ለሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና ስኬታማነት የዩኒቨርስቲ አመራሮች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን ስልጠና የሚሰጡ 30 ዩኒቨርስቲዎች ሰልጣኝ መምህራንንና የትምህርት ቤት አመራሮችን በአግባቡ በመቀበልና በማሰልጠን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
አክለውም የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና ለትምህርት ጥራት ወሳኝ በመሆኑ ዩኒቨርስተዎች መምህራኑና አመራሮቹ የተዘጋጀላቸውን የስልጠና ሞጁል መጨረሳቸውን ፣ስልጠናውንም በአግባቡ መከታተላቸውንና መመዘናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና በአግባቡ እንዲጠናቀቅ የዩኒቨርስቲ አመራሮችና ኃላፊዎች ድጋፍና ትብብር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የተውጣቱ ከ84ሺ የሚበልጡ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች በሚያተምሩት የትምህርት ዓይነት ላይ መሰረት ያደረገ ስልጠና ወስደው ከተመዘኑ በኋላ የምስክር ወረቀት እንደሚሰጣቸው በመድረኩ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ከ52 ሺ የሚበልጡ የ2ኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት ስልጠና መውሰዳቸውንም ይታወሳል፡፡
Aug 01, 2025
27
የትምህርት ሚኒስትሩ በጣሊያን ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት የተማራ ልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፊሰር ብርሃኑ ነጋ በጣሊያን ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA የተመራ ልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ በአገሪቱ ትምህርትን በጥራትና በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የሪፎርም ተግባራት ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
በቀደመው ጊዜ ትምህርትን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ሰፊ ሥራ ቢሰራም የትምህርት ጥራት ተዘንግቶ መቆየቱን ጠቅሰው ይህንንም ከመሰረቱ ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርጸው እየተተገበሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በትምህርት ስርዓቱ የተበላሸውን የሞራል መሰረት ለማስተካከል ሥርዓተ ትምህርቱን ከመቀየር ጀምሮ የፈተና አስተዳደር ስረዓቱን ከስርቆትና ኩረጃ በጸዳ መልኩ በመስጠት የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
ስታንዳርዳቸውን ያሟሉ ትምህርት ቤቶች በጣም ጥቂት መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ከ17 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉንም አንስተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የተማሪ መጽሃፍትን በሁለተኛ ደረጃ አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉንና ከአለም አቀፍ ትብብር ለትምህርት በተገኘ ድጋፍ ተጨማሪ መጽሃፍትን ለአንደኛ ደረጃ ለማሳተምና ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን አብራርተው የጣሊያን መንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የጣሊያን የምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA በበኩላቸው ጣሊያን በኢትዮጵያና በአፍሪካ በተለያዩ የልማት መስኮች ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተው በቀጣይ የዓለም አቀፉ ትብብር ለትምህርት (GPE) መሪነት እንደምትረከብና በዘርፉ ድጋፍ ማድረግ ፍላጎት እንዳላትም ገልጸዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየወሰደቻቸው ያሉ ሪፎርሞችን በአድናቆት እንደሚመለከቱት ገጸው ለተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ እደሚያደርጉ ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፊሰር ብርሃኑ ነጋ በጣሊያን ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA የተመራ ልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ በአገሪቱ ትምህርትን በጥራትና በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የሪፎርም ተግባራት ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
በቀደመው ጊዜ ትምህርትን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ሰፊ ሥራ ቢሰራም የትምህርት ጥራት ተዘንግቶ መቆየቱን ጠቅሰው ይህንንም ከመሰረቱ ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርጸው እየተተገበሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በትምህርት ስርዓቱ የተበላሸውን የሞራል መሰረት ለማስተካከል ሥርዓተ ትምህርቱን ከመቀየር ጀምሮ የፈተና አስተዳደር ስረዓቱን ከስርቆትና ኩረጃ በጸዳ መልኩ በመስጠት የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
ስታንዳርዳቸውን ያሟሉ ትምህርት ቤቶች በጣም ጥቂት መሆናቸውን የጠቀሱት ሚኒስትሩ በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ከ17 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶችን መገንባትና ማደስ መቻሉንም አንስተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የተማሪ መጽሃፍትን በሁለተኛ ደረጃ አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉንና ከአለም አቀፍ ትብብር ለትምህርት በተገኘ ድጋፍ ተጨማሪ መጽሃፍትን ለአንደኛ ደረጃ ለማሳተምና ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን አብራርተው የጣሊያን መንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የጣሊያን የምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት Lia QUARTAPELLE PROCOPIA በበኩላቸው ጣሊያን በኢትዮጵያና በአፍሪካ በተለያዩ የልማት መስኮች ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተው በቀጣይ የዓለም አቀፉ ትብብር ለትምህርት (GPE) መሪነት እንደምትረከብና በዘርፉ ድጋፍ ማድረግ ፍላጎት እንዳላትም ገልጸዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየወሰደቻቸው ያሉ ሪፎርሞችን በአድናቆት እንደሚመለከቱት ገጸው ለተጀመሩ የሪፎርም ተግባራት ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ እደሚያደርጉ ተናግረዋል።
Aug 01, 2025
450
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች በሚኒስቴሩ እና በሀገራችን የ2017 እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም የልማት ዕቅድ እንዲሁም በተቋሙ እየተካሄዱ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞች ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ፣ዘመናዊና የተቋሙን ተልዕኮ በሚገባ የሚፈጽሙ አርኣያነት ያላቸው ሠራተኞች ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሰራተኞች የሚጠበቅባቸውን ተልዕኮ በቅንነትና በብቃት እንዲወጡ ምቹ የሥራ አካባቢ መኖር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም ለማሳካት በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በውይይት መድረኩ የሀገሪቱን የ2018 ዓ.ም የልማት እቅድ ባቀረቡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች የሀገርና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለተጀመሩ ተስፋ ሰጪ የለውጥና ዓበይት ሥራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አንስተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም ጥሩ ውጤት የተመዘገበባቸውን ሥራዎች አስጠብቆ ማስቀጠልና ዝቅተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው ሥራዎችን በልዩ ሁኔታ በመያዝ በቀጣይ በጀት ዓመት በትኩረት እንደሚገባ አጽናኦት ሰጥተዋል፡፡
የሚኒስቴሩ ሰራተኞችም በቀረቡ ሰነዶች ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች በሚኒስቴሩ እና በሀገራችን የ2017 እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም የልማት ዕቅድ እንዲሁም በተቋሙ እየተካሄዱ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞች ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ፣ዘመናዊና የተቋሙን ተልዕኮ በሚገባ የሚፈጽሙ አርኣያነት ያላቸው ሠራተኞች ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሰራተኞች የሚጠበቅባቸውን ተልዕኮ በቅንነትና በብቃት እንዲወጡ ምቹ የሥራ አካባቢ መኖር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ይህንንም ለማሳካት በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በውይይት መድረኩ የሀገሪቱን የ2018 ዓ.ም የልማት እቅድ ባቀረቡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች የሀገርና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለተጀመሩ ተስፋ ሰጪ የለውጥና ዓበይት ሥራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አንስተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም ጥሩ ውጤት የተመዘገበባቸውን ሥራዎች አስጠብቆ ማስቀጠልና ዝቅተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው ሥራዎችን በልዩ ሁኔታ በመያዝ በቀጣይ በጀት ዓመት በትኩረት እንደሚገባ አጽናኦት ሰጥተዋል፡፡
የሚኒስቴሩ ሰራተኞችም በቀረቡ ሰነዶች ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን አንስተው በከፍተኛ አመራሮቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Jul 31, 2025
362
ተባብረን በመትከል ለልጆቻችን አረንጓዴ ሀገር እናስረክባለን፤ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች 700 ሚሊየን የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ የግንፍሌ ወንዝ ዳር ፕሮጀክት አስቀምጠዋል።
በምርሃ ግብሩ ተገኝተው አሻራቸውን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተባብረን በመትከል ለልጆቻችን አረንጓዴ ሀገር እናስረክባለን ያሉ ሲሆን የጎዳናትን ፕላኔት ጥሩ ስራ ሰርተን ምቹ የሰው ልጆች መኖሪያ ለማድረግ መትጋት አለብን ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮች ችግኝ በአንድ ጀንበር የሚለው መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስታ እንደፈጠረባቸው ጠቁመው የሚተከሉት ችግኞች ጸድቀው ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊው እንክብካቤ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
የተተከሉት ችግኞች የአየር ሚዛንን በመጠበቅ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ እንደሚሆንም አክለዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ የሚተከሉት ችግኞች ለአካባቢውን ውበት እንደሚጨምሩ ገልጸው በዚህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስ እንዳሰኛቸው ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች 700 ሚሊየን የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ የግንፍሌ ወንዝ ዳር ፕሮጀክት አስቀምጠዋል።
በምርሃ ግብሩ ተገኝተው አሻራቸውን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተባብረን በመትከል ለልጆቻችን አረንጓዴ ሀገር እናስረክባለን ያሉ ሲሆን የጎዳናትን ፕላኔት ጥሩ ስራ ሰርተን ምቹ የሰው ልጆች መኖሪያ ለማድረግ መትጋት አለብን ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ሚሊዮች ችግኝ በአንድ ጀንበር የሚለው መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስታ እንደፈጠረባቸው ጠቁመው የሚተከሉት ችግኞች ጸድቀው ጥቅም እንዲሰጡ አስፈላጊው እንክብካቤ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
የተተከሉት ችግኞች የአየር ሚዛንን በመጠበቅ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ እንደሚሆንም አክለዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ የሚተከሉት ችግኞች ለአካባቢውን ውበት እንደሚጨምሩ ገልጸው በዚህ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተሳታፊ መሆናቸው ደስ እንዳሰኛቸው ተናግረዋል።
Jul 31, 2025
313
በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 2ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም አተገባበር ያላትን ልምድና የመንግስትን ቁርጠኝነት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አቅርበዋል።
የሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ፖሊሲ ፍሬም ዎርክ በማውጣት ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተግባራዊ በማድረግ የአካባቢ ልማትና ግብርናን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በዚህ የሀገር በቀል የት/ቤት ምገባ ፕሮግራም መንግስት 6.3 ቢሊየን ብርመመደቡንና የማህበረሰቡ ድጋፍ ደግሞ 9.8 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጸው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ ደግሞ 1.3 ቢሊየን መሆኑን አብራርተዋል።
ይህም በኢትዮጵያ ለት/ቤት ምገባ 90 በመቶ የሚደርሰው በጀት በመንግስትና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚሸፈን መሆኑን ገልጸው ተግባሩ የመንግስትንና የማህበረሰቡን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምገባ ፕሮግራሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህፃናት ትምህርታቸው ላይ ትኩረት አድረገው እንዲማሩ ከማድረጉ ባለፈ፤ ጤንነታቸው ተጠብቆ ትምህርታቸው ሳይቋረጥ እንዲማሩ ማድረግ ያስቻለ ተግባር ስለመሆኑም ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከአለም የትምህርት ቤት ምግብ ጥምረት (School Meal Coalition) እና ከአለም የምግብ ፕሮግራም ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው 2ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም አተገባበር ያላትን ልምድና የመንግስትን ቁርጠኝነት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አቅርበዋል።
የሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ ፖሊሲ ፍሬም ዎርክ በማውጣት ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተግባራዊ በማድረግ የአካባቢ ልማትና ግብርናን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል።
በዚህ የሀገር በቀል የት/ቤት ምገባ ፕሮግራም መንግስት 6.3 ቢሊየን ብርመመደቡንና የማህበረሰቡ ድጋፍ ደግሞ 9.8 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጸው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ ደግሞ 1.3 ቢሊየን መሆኑን አብራርተዋል።
ይህም በኢትዮጵያ ለት/ቤት ምገባ 90 በመቶ የሚደርሰው በጀት በመንግስትና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የሚሸፈን መሆኑን ገልጸው ተግባሩ የመንግስትንና የማህበረሰቡን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምገባ ፕሮግራሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህፃናት ትምህርታቸው ላይ ትኩረት አድረገው እንዲማሩ ከማድረጉ ባለፈ፤ ጤንነታቸው ተጠብቆ ትምህርታቸው ሳይቋረጥ እንዲማሩ ማድረግ ያስቻለ ተግባር ስለመሆኑም ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከአለም የትምህርት ቤት ምግብ ጥምረት (School Meal Coalition) እና ከአለም የምግብ ፕሮግራም ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
Jul 29, 2025
239
የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማት እና የዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ አመራሮች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል ተገኝተው አስጀምረዋል።
በክረምት የበጎ ፍቃድ ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ የሀገርን ገጽታ የቀየሩ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን በተለይም የአረንጓዴ አሻራና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቅሰው ሁለተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተጋች ባለች ሀገር እርስ በርስ መተጋገዝና መደጋገፍ ይገባናል ብለዋል።
አክለውም ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል በማስጀመራቸው ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን ሀሳብ አመንጭነት ባልፉት ዓመታት ሲተገብር የቆየው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበጎ ተግባራት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም መተጋገዝን፣ መደጋገፍን፣ መረዳዳትንና መከባበር የበለጠ ለማላቅ እድል የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ሁሉም ኃላፊነቱን በሚገባ ከተወጣ ኢትዮጵያ የያዘችውን የብልጽግና ጉዞ ለሁሉም እኩል እድል በመስጠት ለማሳካት ትልቅ አቅም ይሆናል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር፣ ተጠሪ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በጋምቤላ ክልል ባስጀመሩት በዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ፣ ችግር ላለባቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እና በመትከል ማንሰራራ በሚል ዘንድሮ በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ተጠሪ ተቋማት እና የዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ አመራሮች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል ተገኝተው አስጀምረዋል።
በክረምት የበጎ ፍቃድ ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ የሀገርን ገጽታ የቀየሩ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን በተለይም የአረንጓዴ አሻራና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠቃሽ መሆናቸውን ጠቅሰው ሁለተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተጋች ባለች ሀገር እርስ በርስ መተጋገዝና መደጋገፍ ይገባናል ብለዋል።
አክለውም ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በጋምቤላ ክልል በማስጀመራቸው ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በክቡር ጠቅላይ ሚንስትራችን ሀሳብ አመንጭነት ባልፉት ዓመታት ሲተገብር የቆየው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበጎ ተግባራት መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም መተጋገዝን፣ መደጋገፍን፣ መረዳዳትንና መከባበር የበለጠ ለማላቅ እድል የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ሁሉም ኃላፊነቱን በሚገባ ከተወጣ ኢትዮጵያ የያዘችውን የብልጽግና ጉዞ ለሁሉም እኩል እድል በመስጠት ለማሳካት ትልቅ አቅም ይሆናል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር፣ ተጠሪ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በጋምቤላ ክልል ባስጀመሩት በዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ፣ ችግር ላለባቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እና በመትከል ማንሰራራ በሚል ዘንድሮ በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
Jul 29, 2025
273
የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በመጪው የትምህርት ዘመን እንደሚተገበር ተገለጸ።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል በ2018 ዓ.ም አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በ6 ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
የመርሃ ግብሩ ዓላማ የመምህራንን አጠቃላይ አቅርቦት በማሻሻል ረገድ የሚስተዋሉ እጥረቶችና የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት መሆኑንም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
በአማራጭ የመምህራን የትምህርት መርሃ ግብሩ ከምሁራን ጋር የተመከረበት ፣ በየደረጃው የሚገኙ መምህራንና ሌሎችም የዘርፉ ባለድርሻዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በውይይት ከዳበረ በኋላ መጽደቁን አብራርተዋል።
አማራጭ የመምህራን ትምህርት መርሃ ግብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተገበር ከአሁን በፊት በትምህርት ዙሪያ በትኩረት እንዲሰሩ በተለዩ 6 ዩኒቨርስቲዎችና ክልሎች መላኩን ጠቁመዋል።
ከሁለተኛ ደረጃ መምህራን አቅርቦት ባሻገርም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ላይ ያለውን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል ፕሮግራሙ እንደ አንድ አማራጭ እንዲወሰድ ፍሬም ዎርኩ ለክልሎች እንዲደርስ መደረጉንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ጨምረው ተናግረዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራሙ የመምህራንን አቅርቦት ለማሳደግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፕሮግራሙ በመጪው የትምህርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ላይ በሚሰሩ 6ቱ ዩኒቨርስቲዎች የሚተገበር ቢሆንም ውጤቱ እየታየ እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድም ሃላፊው አክለው ገልጸዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅርቦት ለማሻሻል በ2018 ዓ.ም አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም በ6 ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ ይደረጋል።
የመርሃ ግብሩ ዓላማ የመምህራንን አጠቃላይ አቅርቦት በማሻሻል ረገድ የሚስተዋሉ እጥረቶችና የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት መሆኑንም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
በአማራጭ የመምህራን የትምህርት መርሃ ግብሩ ከምሁራን ጋር የተመከረበት ፣ በየደረጃው የሚገኙ መምህራንና ሌሎችም የዘርፉ ባለድርሻዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በውይይት ከዳበረ በኋላ መጽደቁን አብራርተዋል።
አማራጭ የመምህራን ትምህርት መርሃ ግብሩ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲተገበር ከአሁን በፊት በትምህርት ዙሪያ በትኩረት እንዲሰሩ በተለዩ 6 ዩኒቨርስቲዎችና ክልሎች መላኩን ጠቁመዋል።
ከሁለተኛ ደረጃ መምህራን አቅርቦት ባሻገርም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ላይ ያለውን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል ፕሮግራሙ እንደ አንድ አማራጭ እንዲወሰድ ፍሬም ዎርኩ ለክልሎች እንዲደርስ መደረጉንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ጨምረው ተናግረዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራሙ የመምህራንን አቅርቦት ለማሳደግ የሚያስችል አማራጭ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፕሮግራሙ በመጪው የትምህርት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ላይ በሚሰሩ 6ቱ ዩኒቨርስቲዎች የሚተገበር ቢሆንም ውጤቱ እየታየ እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድም ሃላፊው አክለው ገልጸዋል።
Jul 24, 2025
776
ኢትዮጵያና አልጄሪያ በትምህርትና ስልጠና መስክ ያላቸውን ትብብር ሊያሳድጉ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር መሀመድ ካሊድን በ/ጽቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
ሚንስትሩ ከአምባሰደሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ እየተለወጠ ባለው የአለም ስርዓት ውስጥ አፍሪካውያን ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን በትምህርት ዘርፍ ከአልጄሪያ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው ባረጉት ገለጻ በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን በጋራ ለመስራት ፣የመምህራንና ተማሪዎች ልውውጥ ለማድረግ ፣ የነጻ ትምህርት እድሎችን ለማመቻቸት እንዲሁም የቴክክና ሙያ ትምህርት አሰልጣኞች ስልጠና ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ዶ/ር መሀመድ ካሊድ በበኩላቸው ኢትዮጵና አልጀሪያ በቀጠናዊና አለማቀፋዊ የገራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትብብር ያላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህን ዘርፈ ብዙ ትብብር ማስፋትና ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
አምባሳደሩ በማያያዝ እንደገለጹት የአልጄሪያ መንግስት በኢትዮያ በኩል የሚቀርብለትን የትብብር ፍላጎት መሰረት በማድረግ ስምምነት የመፈራረምና አብሮ የመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር መሀመድ ካሊድን በ/ጽቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
ሚንስትሩ ከአምባሰደሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ እየተለወጠ ባለው የአለም ስርዓት ውስጥ አፍሪካውያን ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን በትምህርት ዘርፍ ከአልጄሪያ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ ከዚሁ ጋር አያይዘው ባረጉት ገለጻ በኢትዮጵያና አልጄሪያ መካል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ከማጠናከር ባለፈ በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮችን በጋራ ለመስራት ፣የመምህራንና ተማሪዎች ልውውጥ ለማድረግ ፣ የነጻ ትምህርት እድሎችን ለማመቻቸት እንዲሁም የቴክክና ሙያ ትምህርት አሰልጣኞች ስልጠና ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር ዶ/ር መሀመድ ካሊድ በበኩላቸው ኢትዮጵና አልጀሪያ በቀጠናዊና አለማቀፋዊ የገራ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትብብር ያላቸው መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህን ዘርፈ ብዙ ትብብር ማስፋትና ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
አምባሳደሩ በማያያዝ እንደገለጹት የአልጄሪያ መንግስት በኢትዮያ በኩል የሚቀርብለትን የትብብር ፍላጎት መሰረት በማድረግ ስምምነት የመፈራረምና አብሮ የመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
Jul 23, 2025
389