News

National News

በኢትዮጵያና በአውሮፓ ህብረት ሀገራት የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር ያለውን የትብብር ግንኙነት ማጠናከር እንደሚገባ ተመላከተ፤ የአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ (ERASMUS +) ትብብር የተዘጋጀ ጉባዔ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የትምህርትና ስልጠና አጋርነት ጥራትና ተገቢነቱን በማሳደግ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል።
በትምህርትና ስልጠና ተቋማት መካከል ግንኙነት በማጠናከር ውጤታማ የልማት ትብብሮችን መተግበር እንደሚገባም ወ/ሮ ሙፈሪሃት አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚና የብሔራዊ ኢራስመስ (ERASMUS +) ተወካይ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው በኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ እኤአ ከ2010 እስከ አሁን ድረስ ከ600 በላይ ኢትዮጵያውያን ነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ የተጀመረው የአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍና ትብብር ጉባኤ ዓላማ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ አገራት ያለውን የትምህርትና ስልጠና ግንኙነት ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ለመምከር መሆኑንም ዶ/ር ኤባ ጨምረው ገልጸዋል።
በአውሮፓ ህብረት የትብብርና አለማቀፋዊነት ልዑክ ሃላፊ ሚስተር ሮቤርቶ ሺሊሮ በበኩላቸው ኢራስመስ (ERASMUS) በትምህርት፣ በስልጠና ፣በወጣቶች በስፖርትና በባህል ላይ አትኩሮ የሚሰራ) የአውሮፓ ህብረት ፕሮግራም መሆኑን አስረድተዋል።
" የትምህርት ሚና በአረንጓዴ ሽግግር" በሚል ርዕስ ዛሬ የተከፈተው ይሄው ጉባኤ እስከ ረቡዕ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን በጉባኤው ላይ 46 ሀገራት (13 ከአውሮፓ ህብረት ሀገራት፣ 32 ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት እና 1 ሰሜን አፍሪካ) የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የትምህርትና ስልጠና አጋርነት ጥራትና ተገቢነቱን በማሳደግ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል።
በትምህርትና ስልጠና ተቋማት መካከል ግንኙነት በማጠናከር ውጤታማ የልማት ትብብሮችን መተግበር እንደሚገባም ወ/ሮ ሙፈሪሃት አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚና የብሔራዊ ኢራስመስ (ERASMUS +) ተወካይ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው በኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ እኤአ ከ2010 እስከ አሁን ድረስ ከ600 በላይ ኢትዮጵያውያን ነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ የተጀመረው የአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍና ትብብር ጉባኤ ዓላማ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ አገራት ያለውን የትምህርትና ስልጠና ግንኙነት ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ለመምከር መሆኑንም ዶ/ር ኤባ ጨምረው ገልጸዋል።
በአውሮፓ ህብረት የትብብርና አለማቀፋዊነት ልዑክ ሃላፊ ሚስተር ሮቤርቶ ሺሊሮ በበኩላቸው ኢራስመስ (ERASMUS) በትምህርት፣ በስልጠና ፣በወጣቶች በስፖርትና በባህል ላይ አትኩሮ የሚሰራ) የአውሮፓ ህብረት ፕሮግራም መሆኑን አስረድተዋል።
" የትምህርት ሚና በአረንጓዴ ሽግግር" በሚል ርዕስ ዛሬ የተከፈተው ይሄው ጉባኤ እስከ ረቡዕ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን በጉባኤው ላይ 46 ሀገራት (13 ከአውሮፓ ህብረት ሀገራት፣ 32 ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት እና 1 ሰሜን አፍሪካ) የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
May 20, 2025 59
National News

የትምህርት ዘርፉን አገራዊ ሪፎርም መሰረት በማድረግ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥና የሪፎርም አጀንዳዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

የስራ አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ይበልጣል አያሌው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የአገር አቀፍ ሪፎርም አካል የሆነው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ይገባል።
በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ለሚገባው የሪፎርም ትግበራ የመዋቅርና የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ እየተደረገ እንደሆነም ዶክተር ይበልጣል አክለው ገልጸዋል።
የአሰራር ማሻሻያውን ተከትሎም አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በአዲስ መልኩ ተሻሽለው እንዲዘጋጁ መደረጉንም ተናግረዋል።
የሙከራ ትግበራው በቅድሚያ በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከዚያም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እስከ ትምህርት ቤቶች ደረጃ በደረጃ በተግባራዊ እንደሚደረግ አመልክተዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርሞርና የማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ ዶ/ር) በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ ሪፎርሞች ተቋማቱ ተልኳቸው በአግባቡ እንዲወጡ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የዩኒቨርስቲዎች ዓላማ ማህበረሰብን መለወጥ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ሠራዊት ተቋማቱ ያሉባቸውን የአሰራር ተግዳሮቶች በመለየት በአፋጣኝ መፍታት እንደሚጠበቅባቸውም ጠቁመዋል።
የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ አቶ ከበደ ግዛው በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ተቋማዊ ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ስራዎች የመልካም አስዳደርና የሪፎርም አጀንዳዎች የአሰራር ስርዓት ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ለመገምገም መሆኑንም አቶ ከበደ ጨምረው ገልጸዋል።
የስራ አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ይበልጣል አያሌው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የአገር አቀፍ ሪፎርም አካል የሆነው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ይገባል።
በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ለሚገባው የሪፎርም ትግበራ የመዋቅርና የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ እየተደረገ እንደሆነም ዶክተር ይበልጣል አክለው ገልጸዋል።
የአሰራር ማሻሻያውን ተከትሎም አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በአዲስ መልኩ ተሻሽለው እንዲዘጋጁ መደረጉንም ተናግረዋል።
የሙከራ ትግበራው በቅድሚያ በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከዚያም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እስከ ትምህርት ቤቶች ደረጃ በደረጃ በተግባራዊ እንደሚደረግ አመልክተዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርሞርና የማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ ዶ/ር) በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ ሪፎርሞች ተቋማቱ ተልኳቸው በአግባቡ እንዲወጡ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የዩኒቨርስቲዎች ዓላማ ማህበረሰብን መለወጥ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ሠራዊት ተቋማቱ ያሉባቸውን የአሰራር ተግዳሮቶች በመለየት በአፋጣኝ መፍታት እንደሚጠበቅባቸውም ጠቁመዋል።
የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ አቶ ከበደ ግዛው በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ተቋማዊ ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ስራዎች የመልካም አስዳደርና የሪፎርም አጀንዳዎች የአሰራር ስርዓት ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ለመገምገም መሆኑንም አቶ ከበደ ጨምረው ገልጸዋል።
May 19, 2025 40
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በአርሜንያ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር የተመራ ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአርሜንያ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር የተመራ ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ እና አርሜንያ ግንኙነት ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑን በማንሳት በትምህርት ዘርፉ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ጥልቅ ሪፎርም በማካሄድ የትምህርት ሥርዓቱን በመቀየር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ፣ ክህሎት ያላቸው፣ ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት በርካታ ሥራዎችን እየሰራች እንደምትገኝ ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልጸዋል።
በተለይም የትምህርት ሥርዓቱን ከፖለቲካ ተጽዕኖ ለማላቀቅ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ረገድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር በቀጣይ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችንም ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም በትምህርት ዘርፉ እየተወሰዱ ባሉ ሪፎርሞች ከሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውንም ለቡድን አባላቱ አብራርተዋል።
የአርሜንያ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር አርቱር ማርቲሮስያን በበኩላቸው አርሜንያና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው አንስተው ይህንን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ እንፈልጋለን ብለዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ በከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲ ግንኙነት፣ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጅነሪግና ሂሳብ (STEM)፣ በጤና ትምህርት ፣ በቴክኒክና ሙያ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ለአርሜንያ ስትራቴጂክ በመሆኗ ለምስራቅ አፍሪካ የትብብር ማዕከል ማድረግ እንፈልጋለን ያሉት ምክትል ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ መንግስታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሁለቱ አካላት በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራንና አካዳሚክ ልውውጥ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ረገድ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም ሰፊ ውይይቶችን አድርገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአርሜንያ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር የተመራ ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ እና አርሜንያ ግንኙነት ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑን በማንሳት በትምህርት ዘርፉ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ጥልቅ ሪፎርም በማካሄድ የትምህርት ሥርዓቱን በመቀየር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ፣ ክህሎት ያላቸው፣ ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት በርካታ ሥራዎችን እየሰራች እንደምትገኝ ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልጸዋል።
በተለይም የትምህርት ሥርዓቱን ከፖለቲካ ተጽዕኖ ለማላቀቅ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ረገድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር በቀጣይ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችንም ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም በትምህርት ዘርፉ እየተወሰዱ ባሉ ሪፎርሞች ከሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውንም ለቡድን አባላቱ አብራርተዋል።
የአርሜንያ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር አርቱር ማርቲሮስያን በበኩላቸው አርሜንያና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው አንስተው ይህንን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ እንፈልጋለን ብለዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ በከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲ ግንኙነት፣ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጅነሪግና ሂሳብ (STEM)፣ በጤና ትምህርት ፣ በቴክኒክና ሙያ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ለአርሜንያ ስትራቴጂክ በመሆኗ ለምስራቅ አፍሪካ የትብብር ማዕከል ማድረግ እንፈልጋለን ያሉት ምክትል ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ መንግስታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሁለቱ አካላት በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራንና አካዳሚክ ልውውጥ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ረገድ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም ሰፊ ውይይቶችን አድርገዋል።
May 14, 2025 42
National News

በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ25 በመቶ በታች ውጤት በሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እርምጃ እንደሚመወሰድ ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ሰው እውቀትና እውነት ፈልጎ የሚመጣባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በተፈጥሮ የተሰጡ የአካባቢው ፀጋዎች ላይ ራዕይ ይዘው መሥራት ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲም በማዕድን ላይ ሰፊ ምርምር በማድረግ ህብረተሰቡን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ሥራ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግን ዋና ተግባራቸው አድርገው መሥራት አለባቸው፦
በዚህ ረገድ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች በመውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች ካስመዘገቡ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።
የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች በተሰጣቸው የተልዕኮ መስክ ልየታ መሠረት ትኩረት አድርገው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የሥነ ምግባር ፋና በመሆናቸው ተማሪዎቻቸውን ማብቃት ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በጥንካሬና በክፍት የተለዩትን ጉዳዮች ያቀረቡት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት የአሰተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ።
ዩኒቨርስቲው ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን በማፍራት ተመራጭ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ራዕይ ይዞ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቡሉሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላትም በአካዳሚክ እና በአስተዳደር ረገድ አሉ ያላቸውን ጥያቄዎች አንስተው ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ሰው እውቀትና እውነት ፈልጎ የሚመጣባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በተፈጥሮ የተሰጡ የአካባቢው ፀጋዎች ላይ ራዕይ ይዘው መሥራት ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲም በማዕድን ላይ ሰፊ ምርምር በማድረግ ህብረተሰቡን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ሥራ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግን ዋና ተግባራቸው አድርገው መሥራት አለባቸው፦
በዚህ ረገድ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች በመውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች ካስመዘገቡ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።
የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች በተሰጣቸው የተልዕኮ መስክ ልየታ መሠረት ትኩረት አድርገው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የሥነ ምግባር ፋና በመሆናቸው ተማሪዎቻቸውን ማብቃት ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በጥንካሬና በክፍት የተለዩትን ጉዳዮች ያቀረቡት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት የአሰተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ።
ዩኒቨርስቲው ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን በማፍራት ተመራጭ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ራዕይ ይዞ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቡሉሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላትም በአካዳሚክ እና በአስተዳደር ረገድ አሉ ያላቸውን ጥያቄዎች አንስተው ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
May 03, 2025 39
National News

የያቤሎ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

ትምህርት ሚኒስቴር ለማስገንባት ካቀዳቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የያቤሎ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በዛሬው እለት ተጀምሯል።
ይህ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ የሚገነባውን ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አስጀምረውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ይህ ሞዴል ትምህርት ቤት አርብቶ አደር በሆነ አካባቢ የሚገነባ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ለሁሉም ዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማዳረስ የምናደርገውን ጥረት ያሳያል ብለዋል።
እንደ ሀገር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ በአለም ላይ ተወዳዳሪ የሆኑ፤ ብቃትና ክህሎት ያላቸው የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት እንደዚህ ያሉ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች ያስፈልጋሉ፤ ለዚህም አቅደን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ከኛ የተሻለ ማሰብ የሚችሉ፣ ሀገር የሚመሩ ተተኪ ትውልዶች ከመንደርና አካባቢ ወጥተው ስለ ሀገር ማሰብ የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የበለጠ መረባረብ አለብን ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን ሲሆን 500 ሚሊየን ብር ይፈጃል ተብሏል።
ትምህርት ቤቱ ግንባታም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ተጠይቋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ለማስገንባት ካቀዳቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የያቤሎ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በዛሬው እለት ተጀምሯል።
ይህ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ የሚገነባውን ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አስጀምረውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ይህ ሞዴል ትምህርት ቤት አርብቶ አደር በሆነ አካባቢ የሚገነባ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ለሁሉም ዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማዳረስ የምናደርገውን ጥረት ያሳያል ብለዋል።
እንደ ሀገር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ በአለም ላይ ተወዳዳሪ የሆኑ፤ ብቃትና ክህሎት ያላቸው የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት እንደዚህ ያሉ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች ያስፈልጋሉ፤ ለዚህም አቅደን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ከኛ የተሻለ ማሰብ የሚችሉ፣ ሀገር የሚመሩ ተተኪ ትውልዶች ከመንደርና አካባቢ ወጥተው ስለ ሀገር ማሰብ የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የበለጠ መረባረብ አለብን ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን ሲሆን 500 ሚሊየን ብር ይፈጃል ተብሏል።
ትምህርት ቤቱ ግንባታም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ተጠይቋል።
May 03, 2025 41
National News

ትምህርት ሚኒስቴር ከሚያስገነባቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የአጋ ጢንጠኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

ሚኒስቴሩ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የሚያስገነባው አጋ ጢንጠኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
ግንባታውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የኦሮሚያ ክልል በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) አስጀምረውታል።
ትምህርት ዓለም ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ በመሆኑ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት ከመሠረቱ በመቀየር ሀገር የሚገነባ ቀጣይ ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ይህ በሻኪሶ ከተማ የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው ያለውን የትምህርት ቤት እጥረት የሚፈታ ይሆናል።
በዚህም የከተማው አስተዳደርና አባገዳዎች ትምህርት ሚኒስቴር ያለውን ችግር በመመልከት ይህንን ትምህርት ቤት ግንባታ በሻኪሶ በማስጀመሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ከአስር እስከ አሥራ ሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር በራሱ ከሚያስገነባቸው ት/ቤቶች በተጨማሪም የ”ትምህርት ለትውልድ'' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማስጀመር ከ80 ቢሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት እንዲደረግላቸው ማድረጉም በመድረኩ ተገልጿል።
በዚህም የኦሮሚያ ክልል ቡኡራ ቦሩ፣ ኢፋ ቦሩ እንዲሁም አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት እና ህብረተሠቡን በማስተባበር በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውም ተብራርቷል።
በተለይም የትምህርት ጥራት ችግርን ከመሠረቱ ለማስተካከል ከ17ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ከሁለት ሚሊየን በላይ ህፃናት እንዲማሩ መደረጉ የተገለፀ ሲሆን።
ክልሉ በትምህርቱ ዘርፍ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥና በሳይንስና ቴክኖሎጂ የዳበሩ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑም ተጠቅሷል።
በክልሉ በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመሩት ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጥራታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በቂ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
ሚኒስቴሩ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የሚያስገነባው አጋ ጢንጠኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
ግንባታውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የኦሮሚያ ክልል በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) አስጀምረውታል።
ትምህርት ዓለም ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ በመሆኑ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት ከመሠረቱ በመቀየር ሀገር የሚገነባ ቀጣይ ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ይህ በሻኪሶ ከተማ የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው ያለውን የትምህርት ቤት እጥረት የሚፈታ ይሆናል።
በዚህም የከተማው አስተዳደርና አባገዳዎች ትምህርት ሚኒስቴር ያለውን ችግር በመመልከት ይህንን ትምህርት ቤት ግንባታ በሻኪሶ በማስጀመሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ከአስር እስከ አሥራ ሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር በራሱ ከሚያስገነባቸው ት/ቤቶች በተጨማሪም የ”ትምህርት ለትውልድ'' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማስጀመር ከ80 ቢሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት እንዲደረግላቸው ማድረጉም በመድረኩ ተገልጿል።
በዚህም የኦሮሚያ ክልል ቡኡራ ቦሩ፣ ኢፋ ቦሩ እንዲሁም አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት እና ህብረተሠቡን በማስተባበር በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውም ተብራርቷል።
በተለይም የትምህርት ጥራት ችግርን ከመሠረቱ ለማስተካከል ከ17ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ከሁለት ሚሊየን በላይ ህፃናት እንዲማሩ መደረጉ የተገለፀ ሲሆን።
ክልሉ በትምህርቱ ዘርፍ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥና በሳይንስና ቴክኖሎጂ የዳበሩ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑም ተጠቅሷል።
በክልሉ በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመሩት ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጥራታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በቂ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
May 02, 2025 35
National News

ሁለም ዜጎች እኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ ከተማ የኡታ ዋዩ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።

በዚሁ ጊዜ የመሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቾን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየገነባ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ኡታ ዋዩ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ በትኩረት እየተሠራ ነው ያሉ ሲሆን፦
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር በርካታ የሪፎርም ተግባራትን ቀርፆ እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገሪቱ ከሌላው አለም ጋር ተወዳዳሪ እንድትሆን፤ ብቁ ተወዳዳሪ፣ ክህሎትን የተላበሱና ግብረ ገብነት የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ በበኩላቸው ትምህርት ሚነስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየሠራ ያለው ሥራ የሚመሰገን መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ ትምህርትን ከመሠረቱ ለመቀየር ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ድረስ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ትምህርት ቤቶችን መገንባት መቻሉን ጠቅሰዋል።
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው ይህ አካባቢ በርካታ ተማሪዎች ያሉበት በመሆኑ አሁን የሚገነባው ትምህርት ቤት የተማሪ ጥምርታን በማስተካከል ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።
በተለይም ግንባታው እንዲጀመር ቦታ በመዘጋጀትና ካሳ በመክፈል የከተማ አስተዳደሩ ለሠራው ሥራ አመስግነው የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስኪጠናቀቅም አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ስታታንዳርዱን ጠብቆ በአስር ወር ይጠናቀቃል የተባለ ሲሆን ለዚህም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የስምምነት ፊርማ ተፈርሟል።
በዚሁ ጊዜ የመሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቾን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየገነባ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ኡታ ዋዩ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ በትኩረት እየተሠራ ነው ያሉ ሲሆን፦
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር በርካታ የሪፎርም ተግባራትን ቀርፆ እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገሪቱ ከሌላው አለም ጋር ተወዳዳሪ እንድትሆን፤ ብቁ ተወዳዳሪ፣ ክህሎትን የተላበሱና ግብረ ገብነት የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ በበኩላቸው ትምህርት ሚነስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየሠራ ያለው ሥራ የሚመሰገን መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ ትምህርትን ከመሠረቱ ለመቀየር ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ድረስ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ትምህርት ቤቶችን መገንባት መቻሉን ጠቅሰዋል።
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው ይህ አካባቢ በርካታ ተማሪዎች ያሉበት በመሆኑ አሁን የሚገነባው ትምህርት ቤት የተማሪ ጥምርታን በማስተካከል ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።
በተለይም ግንባታው እንዲጀመር ቦታ በመዘጋጀትና ካሳ በመክፈል የከተማ አስተዳደሩ ለሠራው ሥራ አመስግነው የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስኪጠናቀቅም አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ስታታንዳርዱን ጠብቆ በአስር ወር ይጠናቀቃል የተባለ ሲሆን ለዚህም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የስምምነት ፊርማ ተፈርሟል።
May 01, 2025 29
National News

ትምህርት ሚኒስቴር በአለታ ጩኮ ከተማ የሚያስገነባው ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጩኮ ከተማ የሚያስገነባውን ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ያለው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንድ ብቻ በመሆኑ ይህ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያለውን ችግር በመፍታትና የተማሪ ክፍል ጥምርታውን በማመጣጠን ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ።
ምቹና መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች መኖር ምቹ መማር ማስተማርን ከመፍጠር ባሻገር ተማሪዎች ትምህርት ቤቶቹን ወደው እንዲመጡም ያደርጋል ተብሏል።
በመድረኩም በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የትምህርት ጥራትን ከመሠረቱ ለመፍታት በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ስታንዳርዳቸውን የጠበቁ 21 የሚሆኑ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው የመማር ማስተማር ሥራ መጀመራቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም ከ86 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት መደረጉ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ትምህርትን በባለቤትነት ለመደገፍ የሚያደረገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።
የተጀመረው የትምህርት ቤት ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀምር ሲሆን ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል ኃላፊነቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲወጣ የስምምነት ፊርማ ተፈራርመዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቂ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ በተመረጡ አካባቢዎች ለመገንባት አቅዶ እየሠራ እንዳለ ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጩኮ ከተማ የሚያስገነባውን ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ያለው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንድ ብቻ በመሆኑ ይህ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያለውን ችግር በመፍታትና የተማሪ ክፍል ጥምርታውን በማመጣጠን ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ።
ምቹና መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች መኖር ምቹ መማር ማስተማርን ከመፍጠር ባሻገር ተማሪዎች ትምህርት ቤቶቹን ወደው እንዲመጡም ያደርጋል ተብሏል።
በመድረኩም በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የትምህርት ጥራትን ከመሠረቱ ለመፍታት በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ስታንዳርዳቸውን የጠበቁ 21 የሚሆኑ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው የመማር ማስተማር ሥራ መጀመራቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም ከ86 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት መደረጉ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ትምህርትን በባለቤትነት ለመደገፍ የሚያደረገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።
የተጀመረው የትምህርት ቤት ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀምር ሲሆን ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል ኃላፊነቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲወጣ የስምምነት ፊርማ ተፈራርመዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቂ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ በተመረጡ አካባቢዎች ለመገንባት አቅዶ እየሠራ እንዳለ ይታወቃል።
May 01, 2025 25
National News

ኢትዮጵያ አዲስ ሥርዓተ ትምህርት በመቅረጽ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ቴክኖሎጂና ክህሎትን የተላበሱ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራች መሆኑ ተገለፀ።

ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 የትምህርት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ የሪፎርምና የፖሊሲ እርምጃዎች ላይ ያላትን ልምድ አካፍላለች።
በመድረኩ ትምህርት ሚኒስቴርን በመወከል ፓናሊስት የነበሩ የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ዮሐንስ ወጋሶ የትምህርት ዘርፉን ለመለወጥ እየተወሰዱ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን አብራርተዋል።
በዚሁ ጊዜ በትምህርት ሥርዓቱ የነበሩ ችግሮችን በሮድ ማፕ በመለየት ኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲዋን ከመቀየር ጀምሮ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የትምህርት ህግ ማጽደቋን ጠቅሰዋል።
በዚህም ትምህርት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ነፃና ግዴታ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።
በተጨማሪም የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ በማድረግ ትምህርቱን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር የ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎትን የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል።
የቱንም ያህል ሥርዓተ ትምህርት ቢቀየር ምቹ የትምህርት ቤት ከባቢን መፍጠር ካልተቻለ ጥራትን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉ ሲሆን፤
ይንንም ለማስተካከል የአዲስ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ዲዛይንና ስታንዳርድ በማዘጋጀት እንዲሁም የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤት መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄን በመላ ሀገሪቱ በማስጀመር ከ80 ቢለየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት በማሰባሰብ ከሰባት ሺህ በላይ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እና በርካታ ነባር ትምህርት ቤቶች እድሳት ማከናወን ተችሏል ብለዋል።
አክለውም ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባን ተግባራዊ በማድረግ ተማሪዎች ምግብ እያገኙ መደረጉን አብራርተዋል።
Innovation Africa 2025 በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በመዲናችን አዲስ አበባ እየተካሄደ እንዳለ ይታወቃል።
ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 የትምህርት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ የሪፎርምና የፖሊሲ እርምጃዎች ላይ ያላትን ልምድ አካፍላለች።
በመድረኩ ትምህርት ሚኒስቴርን በመወከል ፓናሊስት የነበሩ የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ዮሐንስ ወጋሶ የትምህርት ዘርፉን ለመለወጥ እየተወሰዱ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን አብራርተዋል።
በዚሁ ጊዜ በትምህርት ሥርዓቱ የነበሩ ችግሮችን በሮድ ማፕ በመለየት ኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲዋን ከመቀየር ጀምሮ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የትምህርት ህግ ማጽደቋን ጠቅሰዋል።
በዚህም ትምህርት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ነፃና ግዴታ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።
በተጨማሪም የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ በማድረግ ትምህርቱን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር የ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎትን የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል።
የቱንም ያህል ሥርዓተ ትምህርት ቢቀየር ምቹ የትምህርት ቤት ከባቢን መፍጠር ካልተቻለ ጥራትን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉ ሲሆን፤
ይንንም ለማስተካከል የአዲስ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ዲዛይንና ስታንዳርድ በማዘጋጀት እንዲሁም የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤት መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄን በመላ ሀገሪቱ በማስጀመር ከ80 ቢለየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት በማሰባሰብ ከሰባት ሺህ በላይ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እና በርካታ ነባር ትምህርት ቤቶች እድሳት ማከናወን ተችሏል ብለዋል።
አክለውም ሀገር በቀል የትምህርት ቤት ምገባን ተግባራዊ በማድረግ ተማሪዎች ምግብ እያገኙ መደረጉን አብራርተዋል።
Innovation Africa 2025 በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በመዲናችን አዲስ አበባ እየተካሄደ እንዳለ ይታወቃል።
Apr 30, 2025 24
National News

በአፍሪካ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የትምህርት መሰረተ ልማትን ከመገንባት ባለፈ የመምህራንን አቅም መገንባት እንደሚገባ ተጠቆመ።

 
"ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025" የአፍሪካ የትምህርት፣ የኢኖቬሽና ቴክኖሎጂ እና ክህሎት የሚኒስትሮች ስብሰባ "በ21ኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካን ማስተማርና ማብቃት" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተደርጓል።
በዚሁ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ኢትዮጵያ የትምህርት ስርአቱን ለማሻሻልና ጥራትን ለማረጋገጥ ያከናወነቻቸውን ዋና ዋና የሪፎርም ተግባር በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የተደረገው ሀገራዊ ሪፎርም የትምህርት ዘርፉን አካታችነት ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት እኩል የሚስተናገዱበት እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ከለውጡ በፊት የትምህርት ጥራት ችግር እንደነበር ያነሱት ሚኒስትሩ፤ የቅድመ መደበኛ ትምህርት በከተማ ብቻ ተወስኖ ይሰጥ እንደነበርም አንስተዋል፡፡
እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፉ በተደረገው ሪፎርም የቅድመ መደበኛ ትምህርትን በማስፋፋት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየተሠራም ነው ተብለዋል።
በዚህም ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ከ35 ሺህ በላይ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው የቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት በማሻሻል እና በቂ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ረገድ ለተገኘው ውጤት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ነበርም ብለዋል።
ትምህርት ከፍተኛ ሀብት የሚጠይቅ በመሆኑ በመንግሥት አቅም ብቻ የሚሸፈን አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ፤ የሀብት ማሰባሰብ በሁሉም ዜጋ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል፡፡
አክለውም እንደ አፍሪካ የትምህርት ጥራትን በማሻሻል ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ለማፍራት የትምህርት መሰረተ ልማትን ከማሟላት ባለፈ የመምህራንን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል ብለዋለ።
በፓናል ውይይቱም የአንጎላ፣ ዩጋንዳ እና ስዋቶ የትምህርት ሚኒስትሮች በትምህር ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ዜጎችን ማፍራት የሚያስችል አሰራር ተግባራዊ በማድረግ እየሰሩ ያሉትን ስራ አብራርተዋል።
ሚኒስትሮቹ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥና የትምህርት ሥርዓቱን ለመለወጥም ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም ተናግረዋል ።
"ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025" የአፍሪካ የትምህርት፣ የኢኖቬሽና ቴክኖሎጂ እና ክህሎት የሚኒስትሮች ስብሰባ "በ21ኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካን ማስተማርና ማብቃት" በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት ተደርጓል።
በዚሁ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ኢትዮጵያ የትምህርት ስርአቱን ለማሻሻልና ጥራትን ለማረጋገጥ ያከናወነቻቸውን ዋና ዋና የሪፎርም ተግባር በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የተደረገው ሀገራዊ ሪፎርም የትምህርት ዘርፉን አካታችነት ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት እኩል የሚስተናገዱበት እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ከለውጡ በፊት የትምህርት ጥራት ችግር እንደነበር ያነሱት ሚኒስትሩ፤ የቅድመ መደበኛ ትምህርት በከተማ ብቻ ተወስኖ ይሰጥ እንደነበርም አንስተዋል፡፡
እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፉ በተደረገው ሪፎርም የቅድመ መደበኛ ትምህርትን በማስፋፋት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየተሠራም ነው ተብለዋል።
በዚህም ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ከ35 ሺህ በላይ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው የቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት በማሻሻል እና በቂ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ረገድ ለተገኘው ውጤት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ነበርም ብለዋል።
ትምህርት ከፍተኛ ሀብት የሚጠይቅ በመሆኑ በመንግሥት አቅም ብቻ የሚሸፈን አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ፤ የሀብት ማሰባሰብ በሁሉም ዜጋ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ተደርጓል ብለዋል፡፡
አክለውም እንደ አፍሪካ የትምህርት ጥራትን በማሻሻል ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ለማፍራት የትምህርት መሰረተ ልማትን ከማሟላት ባለፈ የመምህራንን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል ብለዋለ።
በፓናል ውይይቱም የአንጎላ፣ ዩጋንዳ እና ስዋቶ የትምህርት ሚኒስትሮች በትምህር ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ዜጎችን ማፍራት የሚያስችል አሰራር ተግባራዊ በማድረግ እየሰሩ ያሉትን ስራ አብራርተዋል።
ሚኒስትሮቹ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥና የትምህርት ሥርዓቱን ለመለወጥም ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም ተናግረዋል ።
Apr 29, 2025 23
National News

የሥርዓተ ትምህርት ሪፎርምን ከመምህራን ሙያዊ ብቃት ጋር ማስተሳሰር እንደሚገባ ተጠቆመ።

Innovation Africa 2025 ጉባዔ በአፍሪካ የሥርዓተ ትምህርት ሪፎርምን ለመተግበር የመምህራን ጥራትና ብቃትን ማረጋገጥ በሚቻልበት ዙሪያ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በመድረኩ ፓናሊስት ሆነው የቀረቡት በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን ትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በትምህርት ዘርፉ የመምህራንን እና የትምህርት ቤት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንዳሉ አንስተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተካሄዱት ሪፎርሞች ውስጥ አንዱ የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ሥርዓተ ትምህርት ከመምህራን ስልጠና ማዕቀፍ ጋር በማጣጣም መምህራንን በተለያዩ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እያሰለጠን እንገኛለን ብለዋል።
በዚህም በባለፈው በክረምት ከ52 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና ስነ ዘዴ ላይ ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
አክለውም በቀጣይ ክረምት 84 ሺ የሚደርሱ መምህራንን በሚያስተምሩት ይዘትና ስነ ዘዴ ላይ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ለመሥጠት እየተሰራ መሆኑንን አንስተው በየትኛውም ሪፎርም ለመምህራን ብቃትና ጥራት ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመድረኩም የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በሥርዓተ ትምህርት ሪፎርም የመምህራንን አቅምና ብቃት ለማሳደግ እየሰሩ ያሉትን ሥራም አጋርተዋል።
Innovation Africa 2025 ጉባዔ በአፍሪካ የሥርዓተ ትምህርት ሪፎርምን ለመተግበር የመምህራን ጥራትና ብቃትን ማረጋገጥ በሚቻልበት ዙሪያ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በመድረኩ ፓናሊስት ሆነው የቀረቡት በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን ትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በትምህርት ዘርፉ የመምህራንን እና የትምህርት ቤት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንዳሉ አንስተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተካሄዱት ሪፎርሞች ውስጥ አንዱ የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ሥርዓተ ትምህርት ከመምህራን ስልጠና ማዕቀፍ ጋር በማጣጣም መምህራንን በተለያዩ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እያሰለጠን እንገኛለን ብለዋል።
በዚህም በባለፈው በክረምት ከ52 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና ስነ ዘዴ ላይ ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
አክለውም በቀጣይ ክረምት 84 ሺ የሚደርሱ መምህራንን በሚያስተምሩት ይዘትና ስነ ዘዴ ላይ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ለመሥጠት እየተሰራ መሆኑንን አንስተው በየትኛውም ሪፎርም ለመምህራን ብቃትና ጥራት ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመድረኩም የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በሥርዓተ ትምህርት ሪፎርም የመምህራንን አቅምና ብቃት ለማሳደግ እየሰሩ ያሉትን ሥራም አጋርተዋል።
Apr 29, 2025 23
National News

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት Innovation Africa 2025 ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል። የትምህርት፣የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከ’ African Brains’ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት Innovation Africa 2025 ጉባኤ በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል መካሄድ ጀምሯል።

በዚህ Innovation Africa 2025 የትምህርት፣ የቴክኖሎጂና ክህሎት ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ሀገራት የዘርፉ ሚኒስትሮችና ልዑካን ቡድን አባላት፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የትምህርት አጋር ድርጅቶች፣ የግሉ ሴክተር ኢንቨስተሮች እየተሳተፉ ይገኛል።
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ቀጣዩን ትውልድ ለመገንባት ትምህርት፣ ቴክኖሎጂና ክህሎት በጣም መሳኝ በመሆናቸው በዚህ ጉባኤ ትርጉም ያለውና የሚተገበር ውይይት እንደሚደረግ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ትምህርትና ክህሎትን ማዕከል በማድረግ በትምህርት ቤት ግንባታና መሠረተ ልማት ማሻሻል፣ በድጂታል ኔትዎርክ ግንባታ እንዲሁም በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።
እንደ አፍሪካ በዚህ ረገድ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ እንስራ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው አሁን ያለንበት የአለም ሁኔታ በጣም የተወሳሰበ በመሆኑ መጪውን ትውልድና ወጣት በትምህርት፣ በቴክኖሎጂና በክህሎት ማዘጋጀት ይጠበቃል ብለዋል።
በመሆኑም ይህ በሦስት ቀን በትምህርት፣በቴኖሎጂና በክህሎት ዘርፍ የምናደርገው ውይይት በትክክል ለአፍሪካ ለውጥ መሠረት የሚጣልበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በጉባዔውም ከትምህርት፣ አይሲቲ እና ከክህሎት ጋር የተያያዙ ወሳኝ አጀንዳዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ይሆናል።
በዚህ Innovation Africa 2025 የትምህርት፣ የቴክኖሎጂና ክህሎት ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ሀገራት የዘርፉ ሚኒስትሮችና ልዑካን ቡድን አባላት፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የትምህርት አጋር ድርጅቶች፣ የግሉ ሴክተር ኢንቨስተሮች እየተሳተፉ ይገኛል።
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ቀጣዩን ትውልድ ለመገንባት ትምህርት፣ ቴክኖሎጂና ክህሎት በጣም መሳኝ በመሆናቸው በዚህ ጉባኤ ትርጉም ያለውና የሚተገበር ውይይት እንደሚደረግ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ትምህርትና ክህሎትን ማዕከል በማድረግ በትምህርት ቤት ግንባታና መሠረተ ልማት ማሻሻል፣ በድጂታል ኔትዎርክ ግንባታ እንዲሁም በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።
እንደ አፍሪካ በዚህ ረገድ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ እንስራ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው አሁን ያለንበት የአለም ሁኔታ በጣም የተወሳሰበ በመሆኑ መጪውን ትውልድና ወጣት በትምህርት፣ በቴክኖሎጂና በክህሎት ማዘጋጀት ይጠበቃል ብለዋል።
በመሆኑም ይህ በሦስት ቀን በትምህርት፣በቴኖሎጂና በክህሎት ዘርፍ የምናደርገው ውይይት በትክክል ለአፍሪካ ለውጥ መሠረት የሚጣልበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በጉባዔውም ከትምህርት፣ አይሲቲ እና ከክህሎት ጋር የተያያዙ ወሳኝ አጀንዳዎች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው ይሆናል።
Apr 28, 2025 26
National News

የመንግስት ትምህርት ቤቶችን ብቃት በማሻሻል ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት ለማድረስ እተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች በ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አድርገዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት የመንግስት ትምህርት ቤቶችን በማብቃት ጥራት ያለው ትምህርት ለዜጎች ሁሉ ለማድረስ እየተሰራ ይገኛል።
በሁሉም መስክ ያለውን ችግር መፍታት የሚቻለው መሀንዲሶች፣ ቴክኖሎጂስቶች፣ ቴክኒሻኖች፣ ቢሮክራቶችና ሌሎችምም ባለሙያዎች በጥራትና በብቃት ማፍራት ሲቻል መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ፣ የመምህራንን አቅም በማሳደግና በሌሎችም የአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች የተጀመሩ ሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጠቅሰዋል።
በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምንም ተማሪ ያላሳለፉ 700 ትምህርት ቤቶችን ለማብቃት ትምህርት ሚኒስቴር እቅድ ይዞ እየሰራ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው በትምህርት ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት እጅግ ትልቁ ተግባር መሆኑን ጠቁመው ከዚህ አንጻር እየተሰራ ያለው ስራ ተስፋ ሰጭ መሆኑን ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም ትምህርት ላይ እየተደረገ ያለው ሪፎርም ሌሎችንም ተቋማት ሊቀይር የሚችል መሆኑን ገልጸው ከቀረበው ሪፖርት ብዙ አበረታች ለውጦች መመልከታቸውን ገልጸዋል።
በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግር ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች ወደትምህርት ቤት እንዲመለሱ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር 9 ወራት እቅድ አፈጻጸምና ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡።
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት የመንግስት ትምህርት ቤቶችን በማብቃት ጥራት ያለው ትምህርት ለዜጎች ሁሉ ለማድረስ እየተሰራ ይገኛል።
በሁሉም መስክ ያለውን ችግር መፍታት የሚቻለው መሀንዲሶች፣ ቴክኖሎጂስቶች፣ ቴክኒሻኖች፣ ቢሮክራቶችና ሌሎችምም ባለሙያዎች በጥራትና በብቃት ማፍራት ሲቻል መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ፣ የመምህራንን አቅም በማሳደግና በሌሎችም የአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች የተጀመሩ ሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጠቅሰዋል።
በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምንም ተማሪ ያላሳለፉ 700 ትምህርት ቤቶችን ለማብቃት ትምህርት ሚኒስቴር እቅድ ይዞ እየሰራ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው በትምህርት ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት እጅግ ትልቁ ተግባር መሆኑን ጠቁመው ከዚህ አንጻር እየተሰራ ያለው ስራ ተስፋ ሰጭ መሆኑን ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም ትምህርት ላይ እየተደረገ ያለው ሪፎርም ሌሎችንም ተቋማት ሊቀይር የሚችል መሆኑን ገልጸው ከቀረበው ሪፖርት ብዙ አበረታች ለውጦች መመልከታቸውን ገልጸዋል።
በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግር ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች ወደትምህርት ቤት እንዲመለሱ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር 9 ወራት እቅድ አፈጻጸምና ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡።
Apr 14, 2025 882
National News

ዩኒቨርሲቲዎች በትክክል የእውቀትና የምርምር ማዕከል በመሆን ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ማፍራት ላይ በትኩረት መሥራት እንዳለባቸው የትምህርት ሚኒስትሩ አሳሰቡ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከጅንካ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

በዚሁ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች በአካዳሚክ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በሚገባ በመወጣት በአለም ሁኔታ እውነተኛ ውይይት የሚደረግባቸውና ለማህበረሰቡ አቅጣጫ የሚሰጡ እውቀቶች የሚፈልቁባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች ለእውነትና እውቀት የሚሰጡት ትኩረት አናሳ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ተማሪዎች ክፍል ከሚማሩት ትምህርት በተጨማሪ አለም አቀፍና ሀገራዊ ሁኔታዎችን እንዲያውቁና ለዛ እንዲዘጋጁ ምሁራዊ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት፤
ስለሆነም ዩኒቨርሲቲዎች በትክክል ልጆች የሚማሩባቸው የእውቀትና የምርምር ማዕከል በመሆን ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ማፍራት ላይ በትኩረት መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የዛሬው ውይይት ዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጣቸው ተልዕኮ አንፃር የሪፎርም ተግባራትን እንዴት እያስኬዱ ነው የሚለውን ለመለየት ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ራሱን የሚችል፣ ሀገሩን የሚጠቅም ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ለማፍራት ዩኒቨርሲቲዎች በውጤት መለካት ይኖርባቸዋል፤ ለዚህም ሚኒስቴሩ ተጠያቂነት የሚያስከትል ስምምነት ከዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር መፈራረሙን ጠቅሰዋል።
በዚሁ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች በአካዳሚክ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በሚገባ በመወጣት በአለም ሁኔታ እውነተኛ ውይይት የሚደረግባቸውና ለማህበረሰቡ አቅጣጫ የሚሰጡ እውቀቶች የሚፈልቁባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች ለእውነትና እውቀት የሚሰጡት ትኩረት አናሳ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ተማሪዎች ክፍል ከሚማሩት ትምህርት በተጨማሪ አለም አቀፍና ሀገራዊ ሁኔታዎችን እንዲያውቁና ለዛ እንዲዘጋጁ ምሁራዊ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት፤
ስለሆነም ዩኒቨርሲቲዎች በትክክል ልጆች የሚማሩባቸው የእውቀትና የምርምር ማዕከል በመሆን ከመንደር አስተሳሰብ ወጥተው ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ማፍራት ላይ በትኩረት መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የዛሬው ውይይት ዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጣቸው ተልዕኮ አንፃር የሪፎርም ተግባራትን እንዴት እያስኬዱ ነው የሚለውን ለመለየት ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ራሱን የሚችል፣ ሀገሩን የሚጠቅም ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ለማፍራት ዩኒቨርሲቲዎች በውጤት መለካት ይኖርባቸዋል፤ ለዚህም ሚኒስቴሩ ተጠያቂነት የሚያስከትል ስምምነት ከዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር መፈራረሙን ጠቅሰዋል።
Apr 12, 2025 694
Recent News
Follow Us