News

National News

A high-level Delegation of the Ministry of Education Led by Berhanu Nega (prof.), the minister, is in Official Visit to Finland

(Nov 07/ 2025) A high-level Ethiopian delegation led by the Minister of Education, H.E. Professor Berhanu Nega, is currently undertaking  official visit to Finland. The visit comes at the official invitation of the Government of Finland.

The delegation is accompanied by Professor Kindeya Gebrehiwot, State Minister of Education, and Mr. Ekugn Ukelo, Head of the Gambella Regional Education Bureau, along with other senior officials of the Finland Embassy in Addis Ababq.

During their stay, the delegation will hold discussions with key Finnish institutions, including the Ministry of Education and Culture, the Ministry of Foreign Affairs, the Finnish National Education Agency, Teacher-Training Schools,  the University of Helsinki,  National Quantom Institute,  Aalto University and Nokia, among others.

The visit aims to strengthen cooperation between institutions in Ethiopia and Finland, enhance experience-sharing in the education and explore opportunities for colloboration in teacher training especially with Kotebe University.

This initiative reflects the Ministry of Education’s continued commitment to improving the quality of education in Ethiopia through international collaboration and knowledge exchange.

ከፊላንድ መንግስት በተላከላቸው ግብዣ መሠረት በክቡር ሚኒስትሩ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በፊንላንድ ጥናታዊ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።
በዚህ ጉብኝትም የትምህርት ሚኒስትሩን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወትና የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ እየተሳተፉ ይገኛል።
የልዑካን ቡድኑ በቆይታው ከፊንላንድ የትምህርትና ባህል ሚኒስትር፣ ከፊላንድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከብሔራዊ የትምህርት ማዕከል፣ እንዲሁም ከሂልሲንኪ ዩኒቨርሲቲና ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችን ጋር ውይይት የሚያደርጉ ይሆናል።
በዚህ ጥናታዊና የልምድ ልውውጥ ጉብኝት ወቅትም በኢትዮጵያና በፊላንድ የትምህርት ተቋማት ሊኖር ስለሚገባው ትብብር እና የፋይናንስ ድጋፍ ተጠናክሮ በሚቀጥልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Nov 07, 2025 24
National News

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልዑካን ቡድን በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፏል።

በትምህርት ሚኒስትሩ የተመራ የልዑካን ቡድን አባላት በሳማርካንድ፣ ኡዝቤኪስታን ሪፐብሊክ በተካሄደው 43ኛው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፎ አድርጓል።
በዚህ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) 43ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በዩኔስኮ ዘርፎች ያከናወነችውን ተግባራት አብራርተዋል።
በዚህም ከትምህርት፣ ከባሕል፣ ከአየር ንብረት ለውጥ እና ከብዝሃ-ሕይወት ዘርፍ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ እየሰራቻቸው ያሉ ሥራዎችን ለጉባኤው አስረድተዋል፡፡
አያይዘውም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተነደፉ ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው ይህ የዩኔስኮ ጠቅላላ ጉባኤ በትምህርት፣ በሣይንስ፣ በባህል፣ ተግባቦትና መረጃ ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ፤ አባል ሀገራትን ለመደገፍ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ውይይቶችን አድርገዋል።
በትምህርት ሚኒስትሩ የተመራ የልዑካን ቡድን አባላት በሳማርካንድ፣ ኡዝቤኪስታን ሪፐብሊክ በተካሄደው 43ኛው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፎ አድርጓል።
በዚህ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) 43ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በዩኔስኮ ዘርፎች ያከናወነችውን ተግባራት አብራርተዋል።
በዚህም ከትምህርት፣ ከባሕል፣ ከአየር ንብረት ለውጥ እና ከብዝሃ-ሕይወት ዘርፍ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ እየሰራቻቸው ያሉ ሥራዎችን ለጉባኤው አስረድተዋል፡፡
አያይዘውም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተነደፉ ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው ይህ የዩኔስኮ ጠቅላላ ጉባኤ በትምህርት፣ በሣይንስ፣ በባህል፣ ተግባቦትና መረጃ ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ፤ አባል ሀገራትን ለመደገፍ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ውይይቶችን አድርገዋል።
Nov 07, 2025 20
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ውጤት ተኮር እንዲሆን ክለሳ እየተደረገበት መሆኑ ተገለጸ፤ ‌‎የሚከለሰው ስርዓተ ትምህርትም በ2018 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርስቲ የገቡ ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ተልዕኮ መሰረት ባደረገ መልኩ ስርዓተ ትምህርቱን የመከለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የዩኒቨርስቲዎቹን ስርዓተ ትምህርት ውጤት ተኮር አድርጎ መከለስ ያስፈለገው የቀድሞዎቹ ስርዓተ ትምህርቶች ዘመኑን ያልዋጁና ከ21ኛው ክፍለ ዘመን ጋር በአግባቡ ያልተቃኙ በመሆናቸው ነው።
‎አዲሱ የውጤት ተኮር ስርዓተ ትምህርት ተመራቂዎች በትምህርት ፕሮግራሞቹ መጨረሻ ሊኖራቸው የሚገባውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት በአግባቡ የፈተሸ መሆኑን መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡
‌‎የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ነገዎ በበኩላቸው ውጤት ተኮር የሆነው ስርዓተ ትምህርት ሙያና ተግባር ተኮር መሆኑን ጠቅሰው ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ምሩቃንን ማፍራት እንደሚያስችል ተናግረዋል።‎
በሁለት ዙሮች እስካሁን 55 የትምህርት ፕሮግራሞች መከለሳቸውን አንስተው እስከ ዓመቱ መጨረሻም ከ80 የሚበልጡ ፕሮግራሞች እንደሚከለሱ አብራርተዋል፡፡
አዲስ የተከለሱት የትምህርት ፕሮግራሞች በ2018 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርስቲ የገቡ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ተግባራዊ እንደሚደረጉም ተጠቅሷል።
‎የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራሞች ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ በሱፈቃድ ሃይለማርያም ለስርዓተ ትምህርት ክለሳው ለቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች መሰረታዊ የሆኑ የተማሪዎች ብቃት መለኪያ (competency) ዝግጅት መከናወኑን ጠቁመዋል።
የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ተልዕኮ መሰረት ባደረገ መልኩ ስርዓተ ትምህርቱን የመከለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የዩኒቨርስቲዎቹን ስርዓተ ትምህርት ውጤት ተኮር አድርጎ መከለስ ያስፈለገው የቀድሞዎቹ ስርዓተ ትምህርቶች ዘመኑን ያልዋጁና ከ21ኛው ክፍለ ዘመን ጋር በአግባቡ ያልተቃኙ በመሆናቸው ነው።
‎አዲሱ የውጤት ተኮር ስርዓተ ትምህርት ተመራቂዎች በትምህርት ፕሮግራሞቹ መጨረሻ ሊኖራቸው የሚገባውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት በአግባቡ የፈተሸ መሆኑን መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡
‌‎የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ነገዎ በበኩላቸው ውጤት ተኮር የሆነው ስርዓተ ትምህርት ሙያና ተግባር ተኮር መሆኑን ጠቅሰው ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ምሩቃንን ማፍራት እንደሚያስችል ተናግረዋል።‎
በሁለት ዙሮች እስካሁን 55 የትምህርት ፕሮግራሞች መከለሳቸውን አንስተው እስከ ዓመቱ መጨረሻም ከ80 የሚበልጡ ፕሮግራሞች እንደሚከለሱ አብራርተዋል፡፡
አዲስ የተከለሱት የትምህርት ፕሮግራሞች በ2018 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርስቲ የገቡ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ተግባራዊ እንደሚደረጉም ተጠቅሷል።
‎የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራሞች ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ በሱፈቃድ ሃይለማርያም ለስርዓተ ትምህርት ክለሳው ለቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች መሰረታዊ የሆኑ የተማሪዎች ብቃት መለኪያ (competency) ዝግጅት መከናወኑን ጠቁመዋል።
Nov 05, 2025 99
National News

በመምህራን የትምህርት ዝግጅትና ልማት ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ።

“Educators shaping futures" በሚል መሪ ቃል በመምህራን የትምህርት ዝግጅትና ልማት ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ የትምህርት ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአለም ባንክና ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በጋራ ባዘጋጀው በዚህ አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የበርካታ ሀገራት የትምህርት ባለሙያዎችና ስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ በመገኘት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ ለትምህርት ጥራት መሳካት መምህራን ቁልፍ ሚና ያላቸው በመሆኑ መምህራንን ማብቃትና መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚና መሆኑን አመላክተው በዚህም የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
መንግስት ለትምህርቱ ዘርፍ በሰጠው ትኩረት በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንና ከነዚህም አንዱ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም መገንባት መሆኑን አንስተው መምህራኑ እውቀትን ከማስተላለፍ ባለፈ ትውልዱ የጽናትና ተስፋ ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀረጽ የሚረዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመከናወን ላይ ያሉት የሪፎርም ስራዎችም የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ከሀገራዊ የልማት ፕሮግራሞች ጋር በማዋደድ እውቀት መር ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚደረጉ ጥረቶችን የሚደግፍ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።
መሠል አለም አቀፍ ምክክሮች ልምድና አሠራሮችን ለማወቅና ለመለዋወጥ በር የሚከፍቱ በመሆኑ ለዝግጅቱ መሳካት ጥረት ያደረጉ ወገኖችንም አመስግነዋል።
የአለም ባንክ ዲቪዥን ዳይሬክተር ሜሪያም ሳሊም በበኩላቸው "Universal Education" ን በ2030 ለማሳካት ዓለማችን ተጨማሪ 44 ሚሊየን መምህራን የሚያስፈልጋት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ለዚህም አዳዲስ መምህራን ወደ ዘርፉ የሚቀላቀሉበትን አማራጮች ማብዛት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የወደፊቱ ትውልድ የሚወሠነው አሁን ላይ ባለን የመምህራን ዝግጅት፣ ብቃትና ልማት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ መምህራንን ማብቃትና መደገፍ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
በጉባኤው 271 ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡእና ከ150 በላይ የሚሆኑ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የዘርፉ ተዋንያኖች የተሳተፉበት መሆኑም ተመላክቷል።
“Educators shaping futures" በሚል መሪ ቃል በመምህራን የትምህርት ዝግጅትና ልማት ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ የትምህርት ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአለም ባንክና ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በጋራ ባዘጋጀው በዚህ አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የበርካታ ሀገራት የትምህርት ባለሙያዎችና ስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ በመገኘት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ ለትምህርት ጥራት መሳካት መምህራን ቁልፍ ሚና ያላቸው በመሆኑ መምህራንን ማብቃትና መደገፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚና መሆኑን አመላክተው በዚህም የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
መንግስት ለትምህርቱ ዘርፍ በሰጠው ትኩረት በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንና ከነዚህም አንዱ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም መገንባት መሆኑን አንስተው መምህራኑ እውቀትን ከማስተላለፍ ባለፈ ትውልዱ የጽናትና ተስፋ ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀረጽ የሚረዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመከናወን ላይ ያሉት የሪፎርም ስራዎችም የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ከሀገራዊ የልማት ፕሮግራሞች ጋር በማዋደድ እውቀት መር ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚደረጉ ጥረቶችን የሚደግፍ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።
መሠል አለም አቀፍ ምክክሮች ልምድና አሠራሮችን ለማወቅና ለመለዋወጥ በር የሚከፍቱ በመሆኑ ለዝግጅቱ መሳካት ጥረት ያደረጉ ወገኖችንም አመስግነዋል።
የአለም ባንክ ዲቪዥን ዳይሬክተር ሜሪያም ሳሊም በበኩላቸው "Universal Education" ን በ2030 ለማሳካት ዓለማችን ተጨማሪ 44 ሚሊየን መምህራን የሚያስፈልጋት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ለዚህም አዳዲስ መምህራን ወደ ዘርፉ የሚቀላቀሉበትን አማራጮች ማብዛት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የወደፊቱ ትውልድ የሚወሠነው አሁን ላይ ባለን የመምህራን ዝግጅት፣ ብቃትና ልማት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ መምህራንን ማብቃትና መደገፍ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
በጉባኤው 271 ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡእና ከ150 በላይ የሚሆኑ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የዘርፉ ተዋንያኖች የተሳተፉበት መሆኑም ተመላክቷል።
Nov 04, 2025 89
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ትኩረት እንዲሰጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ፤ የ2016 ምሩቃን የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ከተያዘው ጥቅምት እስከ መጪው ሚያዚያ ወር እንደሚካሄድ ተጠቁሟል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ማድረግ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
በመደረኩ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የከፍተኛ ትምህርት ተማራቂዎች የመዳረሻ ጥናት የትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ አንዱ መንገድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ፕሮግራሞቻቸውን የመዳረሻ ጥናት ካላካሄዱ ምን እየሰሩ እንደሆነ ለማወቅ እንደሚቸገሩና በገበያው የማይፈለግ የሰው ሀብት ሊያሰለጥኑ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ትኩረት በመስጠት በትምህርት ፕሮግራም ደረጃ ወጥ በሆነ መንገድ ሊሰሩ እንደሚገባ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረ ህይወት በበኩላቸው የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ለፖሊሲ ውሳኔ ፣ ለስርዓተ ትምህርት ክለሳና ለሌሎችም አገራዊ እቅዶች ግብዓት ስለሚሆን በተቀናጀ አግባብ ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በሌላ በኩል የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) የአካዳሚክ ዋና ስራ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች በዚህ ጉዳይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
አያይዘውም የ2016 ተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከጥቅምት እስከ ሚያዚያ 2018 ዓ.ም ድረስ ወጥ በሆነ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መካሄድ እንዳለበትም ዶክተር ኤባ ተናግረዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና አካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች የተገኙ ሲሆን መዳረሻ ጥናትን በሚመለከት ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ማድረግ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
በመደረኩ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የከፍተኛ ትምህርት ተማራቂዎች የመዳረሻ ጥናት የትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ አንዱ መንገድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ፕሮግራሞቻቸውን የመዳረሻ ጥናት ካላካሄዱ ምን እየሰሩ እንደሆነ ለማወቅ እንደሚቸገሩና በገበያው የማይፈለግ የሰው ሀብት ሊያሰለጥኑ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ትኩረት በመስጠት በትምህርት ፕሮግራም ደረጃ ወጥ በሆነ መንገድ ሊሰሩ እንደሚገባ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረ ህይወት በበኩላቸው የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) ለፖሊሲ ውሳኔ ፣ ለስርዓተ ትምህርት ክለሳና ለሌሎችም አገራዊ እቅዶች ግብዓት ስለሚሆን በተቀናጀ አግባብ ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በሌላ በኩል የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የመዳረሻ ጥናት (Tracer Study) የአካዳሚክ ዋና ስራ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች በዚህ ጉዳይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
አያይዘውም የ2016 ተመራቂዎች የመዳረሻ ጥናት በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከጥቅምት እስከ ሚያዚያ 2018 ዓ.ም ድረስ ወጥ በሆነ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መካሄድ እንዳለበትም ዶክተር ኤባ ተናግረዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና አካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች የተገኙ ሲሆን መዳረሻ ጥናትን በሚመለከት ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
Oct 31, 2025 83
National News

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትምህርት ዘርፉን በተመለከተ የምክር ቤት አባላት ያነሷቸውን ጥያቄ መሰረት በማድረግ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ፦

👉🏾ትምህርት ላይ ዋናው ሥራ ቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ላይ ኢንቨስት ማድረግ ነው።
👉🏾በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ክ43 ሚሊየን በላይ የሁለተኛ ደረጃ መጽሃፍትን በማሳተም ለተማሪዎች አንድ ለአንድ ማድረስ ተችሏል።
👉🏾ለመምህራን ጥራት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና በማዘጋጀት በየደረጃው እየተሰጠ ይገኛል።
👉🏾የትምህርት ቤት መገባ ፕሮግራም ወላጆች ሳይጨነቁ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ በእጅጉ አግዟል።
👉🏾በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ትምህርት ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ህዝብ ተባብረው አስደናቂ ተግባር እየፈጸሙ ነው።
👉🏾መንግስት እያካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት በትምህርት ቤቶች አካባቢ ያሉ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን በማስወገድ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጻኦ አበርክቷል፣
👉🏾ልጆቻችን ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ካላደረግን የምንመኛትን ኢትዮጵያ መፍጠር አንችልም በማለት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
👉🏾ትምህርት ላይ ዋናው ሥራ ቅደመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ላይ ኢንቨስት ማድረግ ነው።
👉🏾በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ክ43 ሚሊየን በላይ የሁለተኛ ደረጃ መጽሃፍትን በማሳተም ለተማሪዎች አንድ ለአንድ ማድረስ ተችሏል።
👉🏾ለመምህራን ጥራት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና በማዘጋጀት በየደረጃው እየተሰጠ ይገኛል።
👉🏾የትምህርት ቤት መገባ ፕሮግራም ወላጆች ሳይጨነቁ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ በእጅጉ አግዟል።
👉🏾በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ትምህርት ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ህዝብ ተባብረው አስደናቂ ተግባር እየፈጸሙ ነው።
👉🏾መንግስት እያካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት በትምህርት ቤቶች አካባቢ ያሉ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን በማስወገድ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጻኦ አበርክቷል፣
👉🏾ልጆቻችን ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ካላደረግን የምንመኛትን ኢትዮጵያ መፍጠር አንችልም በማለት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
Oct 28, 2025 79
National News

በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ሰላማዊ መማር ማስተማርን በማስፈን ለተማሪዎች ውጤትና ሥነ-ምግባር መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገለጸ።

ትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል በተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ላይ አግባብነት ካላቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
የውይይት መድረኩን የከፈቱት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የተዘጋጀው ረቂቅ ደንቡ ሰላማዊ መማር ማስተማርን በማስፈን ለተማሪዎች ውጤትና ሥነ-ምግባር መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውኩ ጉዳዮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው ይህንን ለማስተካከል ረቂቅ ደንቡ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ ዜጋ ማፍራት የደንቡ ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ለተግባራዊነቱ ከሚመለከታቸው ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት እንደሚጠበቅ ሚኒስትር ደኤታዋ አሳስበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ እቶ ኡመር ኢማም በበኩላቸው ረቂቅ ደንቡን ለማዳበር በርካታ የውይይት መድረኮች ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በየመድረኮቹ የሚነሱ ሀሳቦች በግብዓትነት ተወስደው ከተካተቱበት በኋላ ረቂቅ ደንቡ ሲጽድቅ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ይደረጋልም ነው ያሉት።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባለፈው ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ መውጣቱንና ይህም ደንብ አዋጁን ለማስፈጸም እየወጡ ካሉ የህግ ማዕቀፎች መካከል አንዱ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቅሷል።
ትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል በተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ላይ አግባብነት ካላቸው ሴክተር መሥሪያ ቤቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
የውይይት መድረኩን የከፈቱት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል የተዘጋጀው ረቂቅ ደንቡ ሰላማዊ መማር ማስተማርን በማስፈን ለተማሪዎች ውጤትና ሥነ-ምግባር መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውኩ ጉዳዮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመምጣታቸው ይህንን ለማስተካከል ረቂቅ ደንቡ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ ዜጋ ማፍራት የደንቡ ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ለተግባራዊነቱ ከሚመለከታቸው ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶና ተናቦ መሥራት እንደሚጠበቅ ሚኒስትር ደኤታዋ አሳስበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ እቶ ኡመር ኢማም በበኩላቸው ረቂቅ ደንቡን ለማዳበር በርካታ የውይይት መድረኮች ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በየመድረኮቹ የሚነሱ ሀሳቦች በግብዓትነት ተወስደው ከተካተቱበት በኋላ ረቂቅ ደንቡ ሲጽድቅ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ይደረጋልም ነው ያሉት።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባለፈው ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ መውጣቱንና ይህም ደንብ አዋጁን ለማስፈጸም እየወጡ ካሉ የህግ ማዕቀፎች መካከል አንዱ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቅሷል።
Oct 24, 2025 728
National News

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡

ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸውን የይዘት አካባቢዎች ማወቅ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዝክስና ባዮሎጂ እንዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡
3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል፤
5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ እንደሚገባ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡
ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸውን የይዘት አካባቢዎች ማወቅ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል። በመሆኑም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዝክስና ባዮሎጂ እንዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡
3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል፤
5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ እንደሚገባ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡
Oct 23, 2025 846
Advertisement

ማስታወቂያ

የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ለፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመምህርነት ለተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤
የጽሁፍ ፈተና በተመረጡ 18 ዩኒቨርስቲዎች ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ መምህራን ጥቅምት 17/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ከታች ከተዘረዘሩት የዩኒቨርስቲ አማራጮች በሚቀርባችሁ ዩኒቨርስቲ በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከዚህ በፊት ከነበረው ስም ዝርዝር በተጨማሪ እንደ አዲስ የተካተታችሁ ስላላችሁ ስማችሁን በድጋሚ በ(https://sbs.moe.gov.et/career/check-status) በመግባት ማረጋገጥ የምትችሉ መሆኑንን እየገለፅን በተጨማሪም የሚቀርባችሁን የፈተና ማዕከል (ዩኒቨርሲቲ) መርጣችሁ እንድታስገቡ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፤ ማንኛውም መምህር ለፈተና ወደ ዩኒቨርስቲ ሲመጣ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መቅረበ ይኖርበታል።
የፈተና መስጫ ማዕከላት (Exam center)
1. ወሎ ዩኒቨርስቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
4. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
6. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
7. ጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ
8. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
9. ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ
10. አሶሳ ዩኒቨርሲቲ
11. ዋቻም ዩኒቨርሲቲ
12. ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
13. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
14. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
15. መቀሌ ዩኒቨርሲቲ
16. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
17. ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ
18. ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ለፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመምህርነት ለተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤
የጽሁፍ ፈተና በተመረጡ 18 ዩኒቨርስቲዎች ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ተፈታኝ መምህራን ጥቅምት 17/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ከታች ከተዘረዘሩት የዩኒቨርስቲ አማራጮች በሚቀርባችሁ ዩኒቨርስቲ በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከዚህ በፊት ከነበረው ስም ዝርዝር በተጨማሪ እንደ አዲስ የተካተታችሁ ስላላችሁ ስማችሁን በድጋሚ በ(https://sbs.moe.gov.et/career/check-status) በመግባት ማረጋገጥ የምትችሉ መሆኑንን እየገለፅን በተጨማሪም የሚቀርባችሁን የፈተና ማዕከል (ዩኒቨርሲቲ) መርጣችሁ እንድታስገቡ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፤ ማንኛውም መምህር ለፈተና ወደ ዩኒቨርስቲ ሲመጣ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መቅረበ ይኖርበታል።
የፈተና መስጫ ማዕከላት (Exam center)
1. ወሎ ዩኒቨርስቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
4. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ
6. ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
7. ጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ
8. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
9. ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ
10. አሶሳ ዩኒቨርሲቲ
11. ዋቻም ዩኒቨርሲቲ
12. ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
13. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
14. ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
15. መቀሌ ዩኒቨርሲቲ
16. አክሱም ዩኒቨርሲቲ
17. ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ
18. ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ
Oct 23, 2025 716
National News

በትምህርት ዘርፉ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና የቅሬታ አፈታት ስርዓቶች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች እና የቅሬታ አፈታት ስራ ክፍል ሃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ በትምህርቱ ዘርፉ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና የቅሬታ አፈታት አሰራር ስርዓቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን የተዘረጉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የቀረበውን የውይይት መነሻ ሀሳብ በመንተራስ ሀሳባቸውን ያጋሩት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በየደረጃው ባለ መዋቅር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ለመፍታት የተለያዩ አደረጃጀቶችና የአሰራር ስርዓቶችን ወደ ተግባር በማስገባት ተገልጋዬችን ከዕንግልት፣ ከተጨማሪ የጊዜና ገንዘብ ወጪ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል።
አሳታፊነት ከማጠናከርና ከማረጋገጥ አኳያ ከዘርፉ ተዋንያን ጋር በጋራ የማቀድ፣ የመከታተል፣ የመገምገምና ግብረ መልስ የመስጠት ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ክብርት ወ/ሮ አየለች አያይዘው ገልጸዋል ።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና የቅሬታ አፈታት ስርዓቶችን ለማሻሻል በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎችን አብራርተዋል።
በተማሪ ቅበላ ፣ በፈተና አስተዳደር፣በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ የመልካም አሰተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ቀድሞ የማወቅና የመከላከል ተግባራት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አያይዘው ገልጸዋል።
በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዬችና የቅሬታ አፈታት መሪ ስራ አስፈጻሚ ፍቅሩ ወርቁ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመከላከልና ለመፍታት በመከናወን ላይ ያሉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የስራ ሀላፊው አያይዘውም በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በኩል የተዘረጉት የመልካም አስተዳደርና የቅሬታ አፈታት አደረጃደትና አሠራር ስርዓቶች ለሌሎች ተቋማት ተሞክሮና ልምድ የሚቀሠምባቸው መሆኑን አመላክተዋል።
ውይይቱ በትምህርቱ ዘርፉ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና የቅሬታ አፈታት አሰራር ስርዓቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን የተዘረጉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የቀረበውን የውይይት መነሻ ሀሳብ በመንተራስ ሀሳባቸውን ያጋሩት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በየደረጃው ባለ መዋቅር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ለመፍታት የተለያዩ አደረጃጀቶችና የአሰራር ስርዓቶችን ወደ ተግባር በማስገባት ተገልጋዬችን ከዕንግልት፣ ከተጨማሪ የጊዜና ገንዘብ ወጪ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል።
አሳታፊነት ከማጠናከርና ከማረጋገጥ አኳያ ከዘርፉ ተዋንያን ጋር በጋራ የማቀድ፣ የመከታተል፣ የመገምገምና ግብረ መልስ የመስጠት ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ክብርት ወ/ሮ አየለች አያይዘው ገልጸዋል ።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና የቅሬታ አፈታት ስርዓቶችን ለማሻሻል በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎችን አብራርተዋል።
በተማሪ ቅበላ ፣ በፈተና አስተዳደር፣በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ የመልካም አሰተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎችን ቀድሞ የማወቅና የመከላከል ተግባራት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አያይዘው ገልጸዋል።
በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደር ጉዳዬችና የቅሬታ አፈታት መሪ ስራ አስፈጻሚ ፍቅሩ ወርቁ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ የሚስተዋሉና የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመከላከልና ለመፍታት በመከናወን ላይ ያሉ የአደረጃጀትና የአሠራር ስርዓቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የስራ ሀላፊው አያይዘውም በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በኩል የተዘረጉት የመልካም አስተዳደርና የቅሬታ አፈታት አደረጃደትና አሠራር ስርዓቶች ለሌሎች ተቋማት ተሞክሮና ልምድ የሚቀሠምባቸው መሆኑን አመላክተዋል።
Oct 22, 2025 575
National News

በኢትዮጵያና በቻይና መንግስታት መካከል በትምህርት መስክ ያለው የትብብር ግንኙነት እየተጠናከረ መምጣቱ ተገለጸ፤ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ዋንግ ዢአዎ የተመራ ልዑካን ቡድን ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነት መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡
በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የትብብር ግንኙነት በአሁኑ ጊዜ ወደ ስትራጂካው አጋርነት መሸጋገሩንም ክቡር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡
የቻይና የስልጣኔ ማዕከል የሆነችው የሻንዢ ግዛት ከኢትዮጵያ ጋር በባቡር ፣ በቴክኒክና ሙያ እና በሌሎችም መስኮች የትብብር ግንኙነት እንዳላትና ትምህርት ሚኒስቴር ከግዛቲቱ ጋር ያለውን ትብብር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍም ማጠናከር እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች መገንባታቸውንና በአሁኑ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጥራት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ግዛቲቱ በሳይንስ ፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም መስኮች ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በግብርና ምርምር ፣ በኢኖቬሽን፣ በትምህርትና በአቅም ግንባታ መስኮች በትብብር በመሰራት ግዛቲቱ ከጅማ ዩኒቨርስቲ ጋር የተፈራረመችው የመግባቢየ ስምምነት በአርአያነት የሚታይ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ዘርፈ ብዙ ስትራቴጂካዊ አጋሮችና ወዳጆች መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ አገራት ግንኙነት በቻይና አፍሪካ ግንኙነትም በግንባር ቀደምነት የሚታይና በማደግ ላይ ላሉ አገራትም በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በሻንዢ ግዛት በኢትዮጵያ በትምህርት መስኩ በተለይም በነጻ የትምህርት እድል ፣ በምርምር፣ በኢንጂነሪንግ ፣ በእርሻ ፣ በህብረተሰብ ጤና እና በሌሎችም የትብብርመስኮች ያለውን ግንኙነት ማጠናከርና ማስቀጠል እንደምትፈልግም አስታውቀዋል።
በዚህ ዓመትም በግዛቲቱ ውስጥ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች 5 ነጻ የትምህርት እድል ለመስተት ዝግጁ መሆኗንም የቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሩዚዳንት ጀማል አባ ፊጣ (ዶ/ር) እና በቻይና የያንግሊንግ አግሪካልቸራል ሃይ-ቴክ ኢንደስትሪያል ዲሞንስትሬሽን ዞን (Agricultural High-Tech Industrial Demonstration Zone, China) ምክትል ጸሀፊ ሚስተር ዋንግ ጁን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ዋንግ ዢአዎ የተመራ ልዑካን ቡድን ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነት መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡
በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የትብብር ግንኙነት በአሁኑ ጊዜ ወደ ስትራጂካው አጋርነት መሸጋገሩንም ክቡር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡
የቻይና የስልጣኔ ማዕከል የሆነችው የሻንዢ ግዛት ከኢትዮጵያ ጋር በባቡር ፣ በቴክኒክና ሙያ እና በሌሎችም መስኮች የትብብር ግንኙነት እንዳላትና ትምህርት ሚኒስቴር ከግዛቲቱ ጋር ያለውን ትብብር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍም ማጠናከር እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ ዩኒቨርስቲዎች መገንባታቸውንና በአሁኑ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጥራት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ግዛቲቱ በሳይንስ ፣ በቴክኖሎጂና በሌሎችም መስኮች ያላትን ልምድና ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በግብርና ምርምር ፣ በኢኖቬሽን፣ በትምህርትና በአቅም ግንባታ መስኮች በትብብር በመሰራት ግዛቲቱ ከጅማ ዩኒቨርስቲ ጋር የተፈራረመችው የመግባቢየ ስምምነት በአርአያነት የሚታይ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ዘርፈ ብዙ ስትራቴጂካዊ አጋሮችና ወዳጆች መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ አገራት ግንኙነት በቻይና አፍሪካ ግንኙነትም በግንባር ቀደምነት የሚታይና በማደግ ላይ ላሉ አገራትም በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በሻንዢ ግዛት በኢትዮጵያ በትምህርት መስኩ በተለይም በነጻ የትምህርት እድል ፣ በምርምር፣ በኢንጂነሪንግ ፣ በእርሻ ፣ በህብረተሰብ ጤና እና በሌሎችም የትብብርመስኮች ያለውን ግንኙነት ማጠናከርና ማስቀጠል እንደምትፈልግም አስታውቀዋል።
በዚህ ዓመትም በግዛቲቱ ውስጥ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች 5 ነጻ የትምህርት እድል ለመስተት ዝግጁ መሆኗንም የቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ሚስተር ዋንግ ዚአዎ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሩዚዳንት ጀማል አባ ፊጣ (ዶ/ር) እና በቻይና የያንግሊንግ አግሪካልቸራል ሃይ-ቴክ ኢንደስትሪያል ዲሞንስትሬሽን ዞን (Agricultural High-Tech Industrial Demonstration Zone, China) ምክትል ጸሀፊ ሚስተር ዋንግ ጁን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
Oct 21, 2025 473
National News

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና” በሚል ርዕስ በተዘገጃ ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና” በሚል ርዕስ በተዘጋጃ ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በተዘጋጀው ሀገራዊ ሰነድና ተዛማጅ ጉዳዬች ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ባጋሩት ሀሳብ እየተቀየረ ያለውን የዓለም ጂኦፓለቲክስ ቀድሞ በመረዳት የሀገራችንን ስትራቴጂያዊ አካሄድና ብሄራዊ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞች ለማረጋገጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ልዩነቶቾን በማጉላት መደነቃቀፍን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች፣አመለካከቶችና ሌሎች ፈተናዎችን በማስወገድ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡
ሀገር ያለ ብሔራዊ ጥቅም ልትቀጥል እንደማትችል አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በጥልቀት መረዳት እንደሚገባም አብራርተዋል።
አክለውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዋና ዋና ፈተናዎች ጂኦስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና እና መልከዓ ምድራዊ የሆኑ ተግዳሮቶች እንደሆኑ አመላክተው እነዚህን ተግዳሮቶች ለመሻገር ዓለም አቀፋዊ ሕጎችን መሠረት በማድረግ ብሔራዊ ጥቅምን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የተፈጥሮ ሀብት፣ የህዝብ ብዛት፣ ጅኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተደራጀ ተቋማዊ አቅምን አስተሳስረን ተለዋዋጭ በሆነው የዓለማችን ሁኔታ ውስጥ ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ተግቶ መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ያለህዝብ ተሳትፎ በመንግሥት ብቻ መሰልና ወሳኝ የሆኑ ብሄራዊ ጥቅሞችን ማስጠበቅም ይሁን ማሳካት የማይችል መሆኑን በመጥቀስ ህዝቡ ከማንነቱ፣ ከህልውናውና ከነገ ተስፋው ጋር የተሳሰረውን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ጆኦስትራቴጂካዊ ቁመና ጉዳይ ላይ በትኩረት ሊመለከተውና ሊሠራበት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በቀረበው ሀገራዊ ሠነድ ላይ ከትምህርት ዘርፉ ሰራተኞች ምን ይጠበቃል በሚለው ጉዳይ ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና” በሚል ርዕስ በተዘጋጃ ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄደዋል፡፡
በተዘጋጀው ሀገራዊ ሰነድና ተዛማጅ ጉዳዬች ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ባጋሩት ሀሳብ እየተቀየረ ያለውን የዓለም ጂኦፓለቲክስ ቀድሞ በመረዳት የሀገራችንን ስትራቴጂያዊ አካሄድና ብሄራዊ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞች ለማረጋገጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ልዩነቶቾን በማጉላት መደነቃቀፍን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች፣አመለካከቶችና ሌሎች ፈተናዎችን በማስወገድ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡
ሀገር ያለ ብሔራዊ ጥቅም ልትቀጥል እንደማትችል አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በጥልቀት መረዳት እንደሚገባም አብራርተዋል።
አክለውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዋና ዋና ፈተናዎች ጂኦስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና እና መልከዓ ምድራዊ የሆኑ ተግዳሮቶች እንደሆኑ አመላክተው እነዚህን ተግዳሮቶች ለመሻገር ዓለም አቀፋዊ ሕጎችን መሠረት በማድረግ ብሔራዊ ጥቅምን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የተፈጥሮ ሀብት፣ የህዝብ ብዛት፣ ጅኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተደራጀ ተቋማዊ አቅምን አስተሳስረን ተለዋዋጭ በሆነው የዓለማችን ሁኔታ ውስጥ ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ተግቶ መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ያለህዝብ ተሳትፎ በመንግሥት ብቻ መሰልና ወሳኝ የሆኑ ብሄራዊ ጥቅሞችን ማስጠበቅም ይሁን ማሳካት የማይችል መሆኑን በመጥቀስ ህዝቡ ከማንነቱ፣ ከህልውናውና ከነገ ተስፋው ጋር የተሳሰረውን ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም ጆኦስትራቴጂካዊ ቁመና ጉዳይ ላይ በትኩረት ሊመለከተውና ሊሠራበት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በቀረበው ሀገራዊ ሠነድ ላይ ከትምህርት ዘርፉ ሰራተኞች ምን ይጠበቃል በሚለው ጉዳይ ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Oct 20, 2025 511
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጲያ UNFPA ተወካይ ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጲያ የUNFPA ተወካይ Mr. Sk Kouameን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ በኢትዮጲያ UNFPA ተወካይ የሆኑት Mr. Sk Kouame UNFPA በሴቶች ትምህርት በተለይም ለሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶችን በማቅረብ እየሰራ መሆኑን በመጥቀስ በቀጣይም ይህንን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
UNFPA ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች ጋር በመተባበር የሴቶችን የትምህርት ሁኔታ በማመቻቸት ረገድ የበለጠ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚፈልጉም ገልጸውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በበኩላቸው UNFPA ውስን በሆነ መልኩ ለሴት ተማሪዎች ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
አክለውም በቀጣይ ከእንዲህ ዓይነት ውስን ድጋፎች ተላቆ በራስ አቅም የሴቶችን ንጽህና መጠበቂያ በማምረት ለኢትዮጵያም ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅም ሥራ መስራት እንደሚገባ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጲያ የUNFPA ተወካይ Mr. Sk Kouameን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ በኢትዮጲያ UNFPA ተወካይ የሆኑት Mr. Sk Kouame UNFPA በሴቶች ትምህርት በተለይም ለሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶችን በማቅረብ እየሰራ መሆኑን በመጥቀስ በቀጣይም ይህንን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
UNFPA ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች ጋር በመተባበር የሴቶችን የትምህርት ሁኔታ በማመቻቸት ረገድ የበለጠ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚፈልጉም ገልጸውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በበኩላቸው UNFPA ውስን በሆነ መልኩ ለሴት ተማሪዎች ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
አክለውም በቀጣይ ከእንዲህ ዓይነት ውስን ድጋፎች ተላቆ በራስ አቅም የሴቶችን ንጽህና መጠበቂያ በማምረት ለኢትዮጵያም ብሎም ለአፍሪካ የሚጠቅም ሥራ መስራት እንደሚገባ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ አብራርተውላቸዋል።
Oct 20, 2025 408
National News

የማጠናከሪያ ትምህር በዕቅድና በትኩረት እንዲመራ ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ

 

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት በአጠቃላይ ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ በተለይም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርትን በዕቅድና በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል።
የተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች፣ ወላጆች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች ጊዚያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ከወዲሁ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ክብርት ወ/ሮ አየለች አስገንዝበዋል።
‎የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በበኩላቸው የማጠናከሪያ ትምህርት ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ጠቀሜታው የላቀ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
‎የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሀንስ ወጋሶ(ዶ/ር) የማጠናከሪያ ትምህርትን በተመለከተ መነሻ ስትራቴጂ እቅድ ያቀረቡ ሲሆን የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከወዲሁ የዕቅድ ክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።
‎በበይነ-መረብ በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችን ፣ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በበይነ መረብ ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት በአጠቃላይ ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ በተለይም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርትን በዕቅድና በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል።
የተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች፣ ወላጆች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተማሪዎች ጊዚያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ከወዲሁ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ክብርት ወ/ሮ አየለች አስገንዝበዋል።
‎የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በበኩላቸው የማጠናከሪያ ትምህርት ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ጠቀሜታው የላቀ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
‎የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሀንስ ወጋሶ(ዶ/ር) የማጠናከሪያ ትምህርትን በተመለከተ መነሻ ስትራቴጂ እቅድ ያቀረቡ ሲሆን የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከወዲሁ የዕቅድ ክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።
‎በበይነ-መረብ በተደረገው በዚሁ ውይይት ላይ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችን ፣ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
Oct 19, 2025 389
Recent News
Follow Us